Quantcast
Channel: ዓለም
Viewing all 231 articles
Browse latest View live

የኢቢሲ ግዞተኞች

$
0
0

በአብዮት ጌታቸው

በአዳራሹ ጥግ የተቀመጠው ሰው ከመድረኩ የተሰየሙት አረጋዊ ላይ ጣቶቹን እየቀሰረ ንግግሩን ቀጠለ፡፡ ‹‹ፕሮፌሰር ቾምስኪ እርስዎ ስለ አሜሪካ ሲናገሩ እኔ ስሰማ እነሆ ዘመናት መጥተው ዘመናት ሄዱ፡፡ ዛሬ ግን ራሴ ጠየቅኩ፡፡ ከፕሮፌሰር ቾምስኪ የእስካሁን ሐሳቦች ምን አተረፍኩ ብዬ? ምላሹም ይኼ ሆነ፡፡ ፕሮፌሰር ቾምስኪ ስለአሜሪካ መጥፎነት ሲገልጹ፣ ፀረዴሞክራሲያዊ መሆን ሲለፉ ከጎናቸው አጫፋሪ ሆኜ መኖሬን፡፡ ከዚህ በኋላ ፕሮፌሰር ስለትውልድ አገሬ መልካም ነገርን መስማት እንጂ መጥፎነቷን ስለማልፈልግ ይህን አዳራሽ ለቅቄ እንድወጣ ይፈቀድልኝ፤›› ብሎ ተሰናበተ፡፡ አረጋዊው ባለ ሙሉ ፕሮፌሰር ከአዳራሹ እየወጣ ያለውን ጠያቂ እየተመለከቱ ምላሻቸውን መስጠት ጀመሩ፡፡ ‹‹እኔ አሜሪካን አልጠላም፡፡ ብጠላት ኖሮ ጠልፎ የሚጥላትን ነገር እየተመለከትኩ በውድቀቷ ጊዜ መሳቅ እችል ነበር፡፡ ግን ለሱ የሚሆን ልብ የለኝም፤›› ለቾምስኪ መውደድ ማለት ችግሮችን ተናግሮ ሙሉነትን መናፈቅ ነውና፡፡ የዚህ ጽሑፍ ዓላማም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ባለፉት ሁለት ዓመታት የመጣበትን መንገድ መዳሰስና ካለበት አጣብቂኝ የሚወጣበትን ነገር በሚመለከተው የመንግሥት አካል እንዲፈለግ ማሳሰብ ነው፡፡

መንደርደሪያ

ትዝ ይለኛል ከአሥር ወራት በፊት አንድ ድርጅቱን የለቀቀ ጋዜጠኛ ስለ ኢቢሲ የወቅቱ አመራሮች የሰላ ትችቱን በማኅበራዊ ድረገጽ አቅርቦ ነበር፡፡ ይህን የአመራሮች አምባገነናዊነት በተለይም የዋና ሥራ አስፈጻሚውን ፀረዴሞክራሲያዊ አካሄድ የሚያሳይ ጽሑፍ በርካታ የድርጅቱ ሠራተኞች አንብበው በሥራ ቦታ ትልቅ መነጋገሪያ አድርገውት ነበር፡፡ በጊዜው ማኅበራዊ ድረገጽ ተጠቃሚ ያልነበሩ ጎልማሶችም በደርግ ወቅት ኦሮማይ ልቦ ለድ እንደተነበበት መንገድ ፕሪንት አድርገው በድብቅ ተቀባብለውታል፡፡ እዚህ ላይ አንባቢ ሊገነዘብ የሚገባው ጉዳይ በኢቢሲ ኤዲቶሪያል ሕግ መሠረት ማንኛውም ሠራተኛ የጣቢያውን ኃላፊዎች ሳያስፈቅድ ስለድርጅቱ ምንም ዓይነት መረጃ በየትኛውም መንገድ ማድረስ አይችልም፡፡ ከዚህ በመነሳትም እንዲህ ዓይነት ጽሑፎች ሲወጡ በአደባባይ ማንበብ የጸሐፊው ደጋፊ ያስብለናል የሚልም ፍርኃት በሠራተኛው ውስጥ መኖሩ በተደጋጋሚ የታየ ጉዳይ ነው፡፡ ይህ ምናልባትም ከአመራሩ አምባገነናዊነት የመነጨ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡

ከላይ የተጠቀሰው በማኅበራዊ ድረገጽ የወጣ ጽሑፍ የድርጅቱ ሠራተኞች ስለ አመራሩ ያላቸውን አመለካከት በጉልህ ያመለከተ ነበር ማለት ይቻላል፡፡

ለዚህ ማሳያ ከሚሆኑ ጉዳዮች መካከል የተለያዩ ሠራተኞች በሐሰት የፌስቡክ አድራሻ የተለያዩ ወቀሳዎችን መሰንዘር መጀመራቸው፣ ቀድመው ድርጅቱን የለቀቁ ታዋቂ ጋዜጠኞች ጽሑፎችን በማኅበራዊ ድረገጾች ላይ በመውሰድ የድጋፍ ሐሳብ መስጠታቸው ሊጠቀስ ይገባል፡፡ ለመሆኑ የመልካም አስተዳደር ቅስቀሳ ልሳን ነኝ የሚለው ኢቢሲ ለምን በራሱ መልካም አስተዳደርን ማስፈን ተሳነው? የድርጅቱ ንቅዘትስ ከየት ተነስቶ የት የደረሰ ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ወደኋላ ያሉ ዓመታትን ለመፈተሸ እንሞክር፡፡

የቀድሞው የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የአሁኑ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በ2006 ዓ.ም. የአመራር ለውጥ በማድረግ የተለያዩ ተግባራትንና ዕቅዶችን ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ድርጅቱ በአዋጅ ቁጥር 858/2006 እንደገና በኮርፖሬሽን መልክ መቋቋሙን ተከትሎ የተለያዩ ሥር ነቀል እንቅስቃሴዎችን እያደረገ መሆኑንና ለማድረግም ማሰቡን በፓርላማ ሪፖርቶች ወቅት አመልክቷል፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ሥር ነቀል የሚል ስያሜ የተሰጣቸው የለውጥ እንቅስቃሴዎች ሁሉን አቀፍ የሆነ መስማማት የተደረሰባቸው ናቸው ወይ ብለን ጥያቄ ስናነሳ ምላሹ አይደለም የሚል ይሆናል፡፡ ግን አሁን ድርጅቱን በመምራት ላይ የሚገኙት ኃላፊዎች ይህን ዓይነት ሐሳብ ያለው ሰው የለውጥ አደናቃፊ በመሆኑ ሊወገድ ይገባል የሚል አስተያየት በድርጅቱ የተለያዩ ስብሰባዎች ወቅት ሲገልጹ ይደመጣል፡፡ ይህ ለምን ሆነ የሚል ጥያቄ ከተነሳ ደግሞ ከላይ ያነሳናቸውን ሁለት መሠረታዊ ጥያቄዎች በውሉ መመለስ ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ አልፎም የአመራሩን ያለፉት ሁለት ዓመታት አካሄዶች ማጤን ግድ ይላል፡፡ በዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ምልከታ በቅርቡ ከኃላፊነታቸው የተነሱት የኢቢሲ ሥራ አስፈጻሚና አመራሮቻቸው የኃላፊነት ዘመን ሦስት መልኮች ያሉት ነው፡፡ የመጀመሪያው ፍፁም ዴሞክራሲያዊ የመሰለ ግን በሐሳብ ተቀናቃኞቻቸው ላይ ዕርምጃ የወሰዱበት ነው፡፡ ሁለተኛው በአንፃሩ ከመጀመሪያው በራቀ መልኩ ኢ-ዴሞክራሲያዊነት የገነነበትና ቡድንተኝነት የጎላበት ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ከዚህ ውጪ ያለውን ሦስተኛ ዘመን ደግሞ በመንታ መንገድ የታጀበ  ይመስላል፡፡ ከላይ የጠቀስናቸውን የኃላፊነት ዘመን ገጽታዎች በተናጠል እየተመለከትን እንቀጥል፡፡

ከሁለት ዓመት በላይ ኢቢሲን የመሩትንና በቅርቡ ከኃላፊነት የተነሱትን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ለመጀመሪያ ጊዜ ሠራተኛው የተዋወቃቸው በዋቢ ሸበሌ ሆቴል በነበረ ስብሰባ ወቅት ነበር፡፡ በጊዜው ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከሠራተኛው ጋር በመሆን ድርጅቱን ለመለወጥ ቁርጠኛ መሆናቸውን ደጋግመው ተናግረዋል፡፡ በቢሮ ውስጥ ያለ ቢሮክራሲ ይስተካከላል፣ ሹመት በዕውቀት ላይ ብቻ የተመሠረተ ይሆናል የሚሉ ሐሳቦችን አንስተዋል፡፡ አብዛኛው ሠራተኛም በተስፋቸው ተስፋውን ዘርቶ ከጎናቸው መሆኑን ተናግሯል፡፡ በእርግጥ በዚህ ጊዜም ቢሆን ሁሌም አዲስ ኃላፊ ሲመጣ እንዲህ የሚል ቃል ነው የሚናገረው፣ ከዚያ ምን የተለየ ተናገሩ በሚል ሥጋቱን ያሰማም አልታጣም፡፡ የሆነ ሆኖ በበርካታ ተስፋዎች የታጀበውና ፍፁም ዴሞክራሲያዊነት የሰፈነበት የመሰለው ጅማሮ ከአፍታ በኋላ የተለያዩ ድምፆች ይሰሙበት ጀመረ፡፡ ለዚህ ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከቀድሞው አመራር ጋር የሠሩ ግለሰቦች  በአግባቡ አልረዱኝም ማለታቸው ነበር፡፡ ይህ ዓይነቱ ልዩነትም ሐሳብን በሐሳብ ከመምታት ይልቅ የሐሳቡን ማደሪያ የሆነውን ግለሰብ ወደ ማጥቃት ተሸጋገረ፡፡ በዚህ ሒደትም የድርጅቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩትና የትምህርታዊ ፕሮግራም ኃላፊ ከሥልጣናቸው መነሳታቸው ተገለጸ፡፡ በወቅቱ ሁለቱ ወገኖች እርስ በርስ መወነጃጀል ቢጀምሩም ከኃላፊነት የተነሱት ሰው ድርጅቱን በመልቀቃቸው፣ ነገሩ ለተወሰነ ወቅትም ቢሆን ተዳፍኖ በደመወዝና መሰል የጥቅማ ጥቅም ወሬዎች ተተካ፡፡

ነገር ግን አሁንም በድርጅቱ አመራር አባላት ውስጥ ያለው የሐሳብ ልዩነት ስለመስፋቱ የተለያዩ መረጃዎች መሰማት ቀጠሉ፡፡ ቀጣዩ ተሰናባችም ሌላው የድርጅቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የስፖርትና መዝናኛ ፕሮግራሞች ኃላፊ፣ አንጋፋ የስፖርት ጋዜጠኛ ሆነ፡፡ የዚህ ሰው ስንብት በበርካታ የክፍሉ ሠራተኞች ላይ ድንጋጤን የፈጠረ ሲሆን፣ በመጨረሻ እሱ ባሸነፈበት ጉዳይ ደመወዙ ታግዶ ለበርካታ ዓመታት ካለበቂ ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም የሠራበትን ቤት በግፍ ተሰናብቷል፡፡

ሌላው የዜናና ወቅታዊ ክልል ኃላፊ የነበረ አንጋፋ ጋዜጠኛም የአመራሩን አካሄድ በመመልከት ራሱን ከሥራ አሰናብቷል፡፡ አሁን በኃላፊነት ላይ ያለውን አመራር የአመራርነት ዘመን የመጀመሪያ መልክ ከተመለከትን የሐሳብ ልዩነቶቹ ሠራተኛው ጋር በውሉ ያልደረሱ ስላልነበሩ፣ ከሞላ ጎደል በሠራተኛው ውስጥ የመግባባት ስሜት ነበር ብሎ መግለጽ ይቻላል፡፡

ይህ ማለት ግን ፈፅሞ ጥያቄ አልነበረም ማለት አይደለም፡፡ ለአብነት ያህል አመራሩ በዚህ ዘመን የቀረውን በቁጥጥር ላይ የተመሠረተ የአመራርነት ጥበብ መጠቀሙ በብዙ ጋዜጠኞች ላይ ቅሬታ አስነስቷል፡፡ ቼክ ሊስት መሙላት፣ በቀን ምን ያህል ዜና ከኤዲተሩ እንደሚደርሰው ለማያውቅ ጋዜጠኛ አዳጋች ሆነ የሰዓት የመውጫና መግቢያ መቆጣጠሪያ አሻራ መተከልና ከደመወዝ ጋር የተገናኘው ማስፈራሪያ መደበኛ ሰዓት ለማይጠብቀው የጋዜጠኝነት ሙያ ዳገት ሆኖ መጣ፡፡ ግን አመራሩ ሁሉንም ያመጣነው ለጋዜጠኛው ተጠቃሚነት በማሰብ ነው፡፡ ከዚህ በኋላ  በቅርብ ጊዜ ባሳያችሁት አፈጻጸም ነው ምደባ የሚካሄደው በመባሉ ሠራተኛው ነገን ተስፋ በማድረግ መብቱን አሳልፎ ሰጠ፡፡ እስከ ምሽት 4፡30 አልያም 6፡00 ሰዓት የሠራ ጋዜጠኛ ሥራው አስገድዶት በነጋታው ማለዳ ሲገባ ቢኖርም፣ አሁን ግን አመራሩ ግዴታ ስላደረገው ጫጫታ መሰማት ጀመረ፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ቅሬታዎች በተለያዩ ተስፋዎች የታጀቡ በመሆናቸው ብዙ ጉልበት የነበራቸው አልሆኑም፡፡ ምናልባትም በዚህ ወቅት የነበረው ተቃውሞ በዚያው በከፍተኛ አመራሩ መሀል የሚሰማ ብቻ ነበር፡፡

ከላይ የተጠቀሰው በተወሰኑ የከፍተኛ አመራሮች ይነሱ የነበሩ የድርጅቱ አካሄድ አግባብ አይደሉም ጥያቄዎች ግን ጊዜያቸውን ጠብቀው ወደ ሠራተኛው መውረድ ጀመሩ፡፡ ሁለተኛ ብለን በጠቀስነው ዘመን ውስጥም ኢ-ዴሞክራሲያዊ የሆኑ ጉዳዮች በረከቱ፡፡ የኢ-ዴሞክራሲያዊ አካሄዶች ነፀብራቅ የሚደረጉት ቡድንተኝነት (ጠባብነት)፣ አምባገነናዊነትና መሰል ጉዳዮች በየቦታው በረከቱ፡፡  በአመራሩ መካከል ያለው የሐሳብ ልዩነትም ጠነከረ፡፡ ለሁለት የተከፈለው አመራር አንዱ አንዱን መውቀስ ሲበዛ፣ ለሥራ አስፈጻሚው ታማኝ የሆነው አመራር በሌሎች ላይ ጣቱን በመቀሰር ለውድቀቱ ሁሉ መነሻ ከቀድሞው አመራር ተልዕኮ የተሰጣቸው አመራሮች ናቸው በማለት ነገሩን ከሐሳብ ሙግት ወደ ፖለቲካዊ ሽኩቻ አዞረው፡፡ በአመራሩ ውስጥ የሐሳብ ልዩነት ያላቸው ግለሰቦች ደግሞ የዋና ሥራ አስፈጻሚው የሚዲያ አመራርነት ዕውቀትና ልምድ ማነስ፣ ለሚዲያው ይዘት ከመጨነቅ ይልቅ ተራ የቢሮ ጉዳዮች ላይ የተጠመዱ መሆን ጣቢያውን ካለበትም ደረጃ የሚያወርድ ነው ማለት ጀመሩ፡፡ እውነት ለመናገር ሥራ አስፈጻሚው በየትኛውም መድረክ ስለሚዲያው ይዘት ትኩረት አለማድረጋቸው እኒህ ሰው መደበኛ የቢሮ ሥራ ላይ ቢቀጥሉ የተሻለ ነበር ያስብላል፡፡ በርካታ የላቀ ሥራ የሚሠሩ ጋዜጠኞች ቢኖሩም ቼክ ሊስት እስካልሞሉ የጣት አሻራ እስካልነኩ ድረስ ጥብቅ ዕርምጃ ውስዱ እያሉ መመርያ በመስጠት፣ ጋዜጠኝነትን ከጥበብ አውርደው ተራ የቢሮ ጉዳይ ብቻ አደረጉት፡፡ በዚህ ምትክ በድርጅቱ የስድስት ወራት ስብሰባ ወቅት ለቢሮው ካፌ ተጠቃሚዎች የተገዛው ወንበርና ጠረጴዛ አጀንዳ ሆኖ የአመራሩ ስኬት ተደረጎ መቅረብ ያዘ፡፡

ይህ ዓይነቱ በአመራሩ ውስጥ ያለ የሐሳብ ልዩነት መስፋትም ሥራ አስፈጻሚው የራሳቸውን ቡድን በመመሥረት ሌሎችን ማዳከም ላይ እንዲበረቱ አደረጋቸው፡፡ በይፋም ለድርጅቱ የፖለቲካ ድርጅት አባላት ከዚህ በኋላ አንታገስም በማለት እንደ አብዮተኞች ከመከላከል ወደ ማጥቃት መዞራቸውን አወጁ፡፡  ከዚህ በኋላ በነበረ የአመራሩ ስብሰባ ላይም ዕርምጃ እወስዳለሁ ሲሉ ማስፈራሪያ ተናገሩ፡፡ እዚህ ላይ ምን ተፈጥሮ እንዲህ ሲሉ ካልን ይኸው ድርጅቱን በዚህ በኩል ብናስኬደው ጥሩ ነው፣ ለምን አላችሁ የሚል የእኔን ብቻ ስሙኝ ስሜት ነው፡፡ ከፍ ብዬ ለመጥቀስ እንደሞከርኩት ይህ የዘመን ገጽታ ፍፁም ኢ-ዴሞክራሲያዊ የሆኑ አካሄዶች የበዙበት ነበር፡፡ ለዚህ ደግሞ አብነት ሆነው ከሚቀርቡ ጉዳዮች መካከል ቡድንተኝነት እየተንሰራፋ መሄዱ ነው፡፡ ሥራ አስፈጻሚው በሐሳብ ከሳቸው የተለያዩትን ከኃላፊነት ካሰናበቱ በኋላ የራሳቸውን ሹመት በተለያዩ ቦታ አድርገዋል፡፡ ከድርጅቱ ወጪም ሰው በማስመጣት በአዲስ አደረጃጀት የይዘት ዘርፍ ኃላፊ በማለት ሹመዋል፡፡ በዚህ ጊዜ በጣቢያው የተለያዩ ወገኖች በአመራሩ ቡድንተኝነት ላይ ሐሳብ መሰንዘር ጀመሩ፡፡

በተለይም የጣቢያው ዋና የሥራ ክፍል የሚባለውን ዜና ክፍል ጨምሮ እስከ ሥራ አስፈጻሚው ድረስ የአንድ ብሔር አባል መሆናቸው፣ ከሌሎች ብሔሮች አቅም ያለው ሰው የለም ማለት ነው የሚል ቅሬታን ውስጥ ውስጡን መናፈስ ቀጠለ፡፡ አንድ የድርጅቱ ጋዜጠኛም ይህን ሐሳብ ለድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ አቀረበ፡፡ የሚገርመው ነገር ይህ ጋዜጠኛ አሁን ከነበረበት ኃላፊነት ተነስቷል፡፡ ምክንያት ከሚደረጉ ጉዳዮችም በአብዛኛው ሠራተኛ ዕምነት ትልቁን ቦታ የሚይዘው ይኼው በአደባባይ ይህን ሐሳብ ማፍረጥረጡ ነበር፡፡ ከዚህ ግለሰብ በተጨማሪም በጊዜው የዜናና ወቅታዊ ክፍል ኃላፊ የነበረው ሰው የግለሰቡ ጥያቄ ትክክል ነው፣ ከአንድ ብሔር በዝተናል የሚል ሐሳብ በመሰንዘሩ ተቃውሞው ከሌሎች ነገሮች ጋር ተዳምሮ ከኃላፊነት ለመነሳቱ ምክንያት እንደሆነ በሠራተኛው ይታመናል፡፡

የአመራሩ ኢ-ዴሞክራሲያዊነት ግን በእንዲህ ዓይነት ብቻ የሚገለጽ አይደለም፡፡ ይልቁንም ሥራ አስፈጻሚው ከመድረክ ሆነው ድራማዊ በሚመስል መልክ ራሳቸውን ተገምጋሚም አሰገምጋሚም  ባደረጉበት ወቅት አንድ አንጋፋ ጋዜጠኛ በሐሳብ ብዝኃነት የማያምኑ አምባገነን ነዎት ስትል ገልጻቸዋለች፡፡ ረጅም ሕይወትን በትግል ያሳለፈ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ራሴን አሳልፌ ሰጠሁ ከሚል ሰው የማይጠበቅ አምባገነንት አለብዎት ብላቸውም ነበር፡፡ ይህን ሐሳብ በጊዜው ከፍተኛ ኃላፊነት ላይ ያሉ ሌሎች አመራሮችም ደጋግመው በዚህ ግምገማ ወቅት አንስተውላቸዋል፡፡ ራሳቸውን ቁጭ ብለው ዕድል እየሰጡ ሲገመገሙት ለአመራሩ አጥጋቢ መልስ ሳይሰጡ ተሰናብተዋል፡፡

ሌላው የዚህ ዘመን ገጽታ ተደርጎ የሚመጣ ጉዳይ አዲስ የተሾሙ አመራሮች ኢ-ዴሞክራሲያዊ አካሄድ መጎልበት ነው፡፡ በዚህ ውስጥ በአሁኑ ወቅት በድርጅቱ በከፍተኛ ኃላፊነት ላይ የሚገኙት የተለያዩ ኃላፊዎች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ እነዚህ ኃላፊዎች በዘፈቀደ የፈለጋቸውን የማድረግ መብቱ የታደላቸው ሲሆን፣ የሚፈልጉትን ሰው በቴሌቪዥን ስክሪን እንዲያቀርብ መፍቀድ ያልፈለጉትን ያላሳማኝ ምክንያት ከስክሪን ማውረድ ይችላሉ፡፡ ይህ ዓይነቱ አካሄድም አንዳንዴ ወደ አክራሪነት የተጠጋ ሲመስል ተስተውሏል፡፡ ለአብነት ያህል አንዲት ኃላፊ እኔ በምመራቸው ክፍሎች ዲያቆን ዳንኤል ክብረት እንዳይቀርብ የሚል ዕገዳ መጣሏ ይታወሳል፡፡

ለምን የሚል ጥያቄ ቢቀርብም ውኃ የሚያነሳ ክርክር ማድረግ አልቻለችም፡፡ በነገራችን ላይ በዚች አመራር ላይ የተለያዩ ጋዜጠኞች የአቅም ውስንነት አለባት ብለው ለዋና ሥራ አስፈጻሚው አቤቱታ ቢያቀርቡም፣ እዚያው ታገሏት የሚል ምላሽ ከማግኘት ውጪ መፍትሔ አላገኙም፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ዘንድ ገብተው ቅሬታ ያቀረቡ ጋዜጠኞችም በጊዜው የተለያዩ ውንጀላዎች የተሰነዘረባቸው ሲሆን፣ ቢሮዬ 24 ሰዓት ክፍት ነው ከሚሉ አመራር ደጃፍ ደርሶ ቅሬታ ማቅረብ በሠራተኞቹ ዓመታዊ ግምገማ ወቅት ዋና ጉዳይ ተደርጎ ተጠይቀውበታል፡፡

ይህ ሁለተኛው መልክ የአመራሩ ዘመን የስፖርት ክፍል ታዋቂ ጋዜጠኞች ተጠራርገው የለቀቁበት፣ ለመልቀቂያ ሲመለሱም በጣቢያው የመልካም አስተዳደር ችግር እንደሌለ ፈርሙ የተባሉበት፣ የጣቢያው ዶክመንተሪ ክፍል ሥራ የተቀዛቀዘበት ኃላፊውም በሚደርሰባቸው ጫና ተቋሙን የለቀቁበት ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የጣቢያው ኤዲቶሪያል ፎረም ድርጅቱን ለመቀየር በሚል ሰበብ ፓይለት ፕሮጀክት በዜናና ወቅታዊ ክፍል ብቻ በመተግበር በሐሳብ ልዩነት የቆመውን የክፍሉ አመራር በማንሳት፣ የፓይለት ፕሮጀክቱ አስተባባሪ የነበሩ ከላይ የጠቀስናቸው ግለሰብ አመራር ወደ ሥልጣን መምጣታቸው ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ይህን ተከትሎ ስብሰባ የጠራው አመራሩ የእነዚህን ረጅም ዓመታት  በጋዜጠኝነትና በኃላፊነት የመሩ ግለሰብ ከኃላፊነት መውረድ ግዳይ እንደጣለ ጀግና በታላቅ ፉከራና ማስፈራሪያ ማቅረቡ አስገራሚ ነበር፡፡ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ዘገባ ወቅት ጓደኞቻቸው በጦር ሜዳ ሲያልፉ በሕይወት ተርፈው የመጡና በኃላፊነት ረጅም ዘመን የመሩን ሰው ስንብት የግለሰቡን ሰብዕና በሚዘልፍ ቃላት ማቅረብ በእርግጥም አስገራሚም አሳፋሪም ነበር፡፡ በዚህ ወቅት ከተነሱ ጥያቄዎች መካከል በስድስት ወሩ ግምገማ የተሻለ አፈጻጸም ነበረው የተባለ ሰው ከኃላፊነት ለምን ወረደ? ከሥራ ውጪ መሥፈርት አላችሁ ወይ? ተብለው ቢጠየቁም ለመልስ ያህል አደባብሰው ለማለፍ ሞክረዋል፡፡

ሦስተኛው የኃላፊነት ዘመን ገጽታ ባለፉት ወራት የዚህ አመራር ተግባራት ላይ ያተኩራል፡፡ ይህ ዘመን ከላይ እንደተጠቀሰው ሁለት ገጽታዎች ያሉት ነው፡፡ የመጀመሪያው በአመራሩ ውስጥ ያለው የሐሳብ ልዩነት እንደገና በሌሎች ሰዎች መሪነት መቀስቀሱ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በሠራተኛውና በአመራሩ መካከል ያለው ልዩነት ከምንጊዜውም በላይ እየሰፋ መሄድ ነው፡፡

የመጀመሪያውን ነጥብ በማንሳት እንቀጥል፡፡ ይህ አመራር በአንድ ሐሳብ መኖር እንጂ በሐሳብ ብዝኃነት የሚያምን አይመስልም፡፡ በመሆኑም ከላይ የሆኑት ሁሉ ሆነዋል፡፡ ከዚህ ለመውጣትም ተመሳሳይ ሐሳብ ሊያራምዱ የሚችሉ፣ ስህተት ነውን የማያወቁ ሰዎችን ወደ መሾም ተዘዋውሯል፡፡ ነገር ግን በዚህ መንገድም ቢሆን ሐሳብ ማዳፈን አለተቻለም፡፡ ለዚህ ማሳያ የሚሆነው ከኦሮሚያ ቲቪ መጥቶ በከፍተኛ አመራርነት የተሾመ ግለሰብ ድንገት ከቢሮ መጥፋትና ስልክ ሲደወል ለንደን መኮብለሉ መሰማቱ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ዳይሬክተር ከአገር መውጣት አመራሩን ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ የከተተ ጉዳይ ነበር፡፡ በዚህ ውስጥ የሚካተተው ሌላው ጉዳይ የዚሁ አመራር አካል ሆነው ሥራ አስፈጻሚውን በድፍረት የሞገቱ  መፈጠራቸው ነበር፡፡ ለምሳሌ የኢቢሲ የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ በአንድ ስብሰባ ላይ ይህን ብናገር ከኃላፊነት እንደምነሳ አወቀዋለሁ፣ ግን ተናግሬ ልነሳ ብላ ነበር፡፡ እንዳለችውም አሁን ከኃላፊነት ተነስታለች፡፡

ሁለተኛውን ነጥብ ለማንሳት እንሞክር፡፡ በዚህ አመራር ሦስተኛ ገጽታ ውስጥ የሚካተተው ይህ ነጥብ በአመራሩና በሠራተኛው መካከል ልዩነቱ እየሰፋ መሄዱን ያሳየናል፡፡

ከወራት በፊት በድርጅቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ዋና ሥራ አስፈጻሚው በተገኙበት ስብሰባ ተደርጎ ነበር፡፡ በዚህ ስብሰባ ወቅት በርካታ ሠራተኞች ቅሬታቸውን ያሰሙ ሲሆን፣ የተጋነነው የአመራሩ የጥቅማ ጥቅም ጉዳይና መሰል ሐሳቦች ትልቅ ቦታ ይዘው ነበር፡፡ ይህ ስብሰባ ለመጀመሪያ ጊዜ ሥራ አሰፈጻሚውን ከተዋወቅንበት የሸበሌ ሆቴሉ ጋር ከተነፃፀረ አመራሩ ከየት ተነስቶ የት እንደደረሰ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ ከቡድን መሪ ጀምሮ እስከ ሥራ አስፈጻሚ ደርሶ በገንዘብና በዓይነት የተለቀቀው ጥቅማ ጥቅም የሠራውንና ባለቤት የሆነውን ጋዜጠኛ ያገለለ ሆነ፡፡ በወቅቱ ለምን ሠራተኛው ይበደላል የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ሥራ አስፈጻሚው፣ ለእኔ ሠራተኛ ማለት ከምክትሌ ጀምሮ ያለው ስለሆነ ጥቅማ ጥቅም እንደተደረገላችሁ ነው የማውቀው የሚል አስቂኝ መልስ ሰጥተዋል፡፡ ኃላፊው በዚህ ሳይበቃም ኃይል የተቀላቀለባቸው ንግግሮችን በማሰማት ዛቻም አስተላልፈዋል፡፡ ከዚያ በፊት እንደሚሉት ሁሉ ለመውጣት የምታስቡ ድርጅቱን ልቀቁ ሲሉ ከአንድ ከመሪ የማይጠበቅ ንግግር ተናግረዋል፡፡

የድርጅቱን 50ኛ ዓመት ምሥረታ በ51 ዓመቱ ያከበረው ቀርፋፋ አመራር፣ በድርጅቱ ታሪክ ውስጥ ያለፉ ታላላቅ ሰዎችን ዘንግቶ የራሱን አመራር ዘመን ሲያወድስ ተሰምቷል፡፡ ኢቢሲ ሁለት ዓመቱን ያከበረ ይመስል ባለፉት ሁለት ዓመታት በሚል አሳፋሪ የታሪክ ሽሚያ ውስጥ የገባ አመራር መሆኑን አመልክቷል፡፡ በጅማና ድሬዳዋ ጊዜያዊ ስቱዲዮ ባልሠራበት ሁኔታ በ“DSNJ” የሚያስተላልፈውን ዘገባ ከጊዜያዊ ስቱዲዮ በማለት ሕዝብን በማታለልም ዛሬም ድረስ ዘልቋል፡፡

የዚህን አመራር ግራ የተጋባ አካሄድ የሚያሳዩ ጉዳዮችን በመግለጽ ጽሑፌን ልቋጭ፡፡ ይህ አመራር በመጣ ጊዜ ለተነሱ ችግሮች የቆየው አመራር የተከለው ችግር ነው ሲል ቆይቷል፡፡ እነዚህ ችግሮች ሳይፈቱ ሲቀሩም የተዘረጋውን ሲስተም የሚያበላሹ ሰዎች መብዛት በማለት ነገሩን ከራስ ለማራቅ ሞክሯል፡፡

በዚህ መልክም ትንሽ ተጉዞ ጥያቄ ሲበረክት ስትራቴጂካዊ ፕላኑ ይፈታዋል የሚል የተስፋ እንጀራ ጋግሯል፡፡ ለመሆኑ ስትራቴጂካዊ ፕላኑ ምን ጨምሮ መጣ? የመጀመሪያው የደመወዝ ጭማሪ ለሠራተኛው ማድረጉ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ ያሉ ጉዳዮች ግን በተቃራኒ አሉታዊ ተደርገው ይጠቀሳሉ፡፡ ለአብነት ያህል የራዲዮ ዜና ኃላፊ በቡድን መሪ፣ የቴሌቭዥን በዳይሬክተር ሲመሩ ላየ አመራሩ ሥራን ሳይሆን ሰውን ታሳቢ ያደረገ ነው የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ከኃላፊነት የተነሱ አመራሮችን ቅሬታ ለማፈን ወደ ትምህርት መላኩ ማሳያ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ ለትምህርት መላክ ደግሞ ተፈላጊ ሰዎችን በቦታቸው ለማስቀመጥ የተደረገ መሆኑ የሚታወቀው፣ በኢቢሲ ሁለተኛ ዲግሪ የተማረ ሰው ከቦታው እንዲነሳ ስለተፈለገ ብቻ በድጋሚ እንዲማር ተገዷል፡፡

አንድ ጊዜ እንኳን ለመማር ዕድል ብርቅ በሆነበት ቤት ለአንድ ሰው ደጋግሞ የመማር ዕድል መስጠት ምን ያህል ሌላን ያም ይሆን?

በዚህ ምዕራፍ ውስጥ ትልቅ ቦታ ከሚይዙ ጉዳዮች መካከል ከወራት በፊት በስትራቴጂካዊ ፕላኑ ዋዜማ ሰሞን በድርጅቱ ያልታሰበ ሹመት ለበርካቶች ተሰጥቶ ነበር፡፡ በጊዜው ስትራቴጂካዊ ፕላኑ አለቀ እያለ ለነበረ አመራር ይህን ማድረጉ የፕላኑ አንድ አካል ይመስል ነበር፡፡ ግን አይደለም ከጥቂት ወራት በፊት ሹመት ተሰጥቷቸው መኪና ተረከቡ የተባሉ አመራሮች ከሰሞኑ በስትራቴጂካዊ ፕላኑ ከኃላፊነት መነሳታቸው የተሰማው የጥቂቶች አይደለም፡፡ ይህ ለምን ሆነ ስንል ምክንያት አልባ የዘፈቀደ የአመራር ጥበብ ውጤት ነው፡፡

አሁን ኢቢሲ ብትሄዱ ሁለት ብሶቶች የሚሰሙ ይመስለኛል፡፡ የመጀመሪያው ካለምንም በቂ ጥናት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮና ቋንቋዎች ሥርጭት ክፍል ለሥራ ይሁን ለግዞት ወደ ዘነበወርቅ ግቢ ይምለስ መባሉ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በስትራቴጂካዊ ፕላኑ ያለበቂ ዕወቅትና ልምድ የተሸሙ ሰዎች መበርከት ነው፡፡ ሁለቱም ለእኔ ተመሳሳይ የዜሮ ድምር ጨዋታዎች ናቸው፡፡ በዚህ መሀል የሚጉላላው ሠራተኛ ግን አሁንም ያሳዝናል፡፡ መልካም አስተዳደር በሚሰብክ ጣቢያ መልካም አሰተዳደር መጠማት ይገርማል፡፡ ይህ ዓይነቱ አካሄድም የጋንግሪን ያህል እየሰፋ ሳይሄድ ቶሎ ሊታረም ይገባል፡፡ የድርጅቱ ሠራተኛ በነፃነት ሊናገርበት የሚችል መድረክ ተፈጥሮ ችግሮች ሊፈቱ ያስፈልጋል፡፡ ያለበለዚያ ለዋና ሥራ አስፈጻሚው ሽኝት ለዚህ ሹመት ያበቁን እሳቸው ናቸው በሚል ከ500 ብር በላይ ያወጡ ሰዎች የሚቦርቁበት ቤት መሆኑ ይቀጥላል፡፡

ኑሮ በኢቢሲ እንዲህ ነው፡፡ ሁለት ዓመት ሙሉ ግዞት የበዛበት የደመወዝ ጭማሪ ያልገታው ፍልሰት ያለበት የብዝኃነት ድምፅ ብሎ እየለፈፈ የብዙኃን ድምፅ የማይሰማበት፡፡ ከሁሉም ከሁሉም የሮበርት ግሪንን “48 Law of Power” (48 የሥልጣን ላይ መሰንበቻ መንገዶች) በውሉ ያልተረዱ ቀሽም አንባቢዎች የበዙበት ግን እሱን ለመተግበር የሚጥሩበት መንደር፡፡ ኢቢሲ፡፡

ከአዘጋጁ፡-ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

 

Standard (Image)

‹‹ኧረ የሕግ ያለህ!!››

$
0
0

በአካል ጉዳተኛው

መንግሥታት ይብዛም ይነስም በሌላ በማንኛውም አካል ሊከናወኑ የማይችሉ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ አገልግሎቶችን ለሕዝባቸው ያቀርባሉ፡፡ ይህን ተኪ የሌለውን ሥራ ለማስፈጸም የሚችሉት ደግሞ ብቃትና ጥራት ያለው ሲቪል ሰርቪስ በመፍጠር ነው፡፡ ‹‹ሲቪል ሰርቪስ›› የሚለው የእንግሊዝኛ ቃል ሲሆን ጥሬ ትርጉሙ ‹‹የሕዝብ አገልጋይ›› ማለት ነው፡፡ በአገራችን የነበሩት መንግሥታት በባህሪያቸው ለሕዝብ ተጠሪና የሕዝብ አገልጋይ ባለመሆናቸው፣ የመንግሥት ሠራተኛ የሚመራበት አሠራርና አደረጃጀት አልነበራቸውም፡፡ የመንግሥት ሠራተኛው አመለካከት ራሱን የሕዝብ ተቀጣሪና አገልጋይ አድርጎ እንዲቆጥር ሳይሆን፣ የሕዝብ የበላይ ተቆጣጣሪና ተገልጋይ አድርጎ እንዲቆጥር የሚያደርገው ነበር፡፡

ከ1983 ዓ.ም በኋላ ያለው መንግሥት ሲቪል ሰርቫንቱ የሕዝብ አገልጋይነት ስሜቱን እንዲያዳብርና በሕዝብ የተመረጠ መንግሥት የሚያወጣቸውን ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመተግበር የተለያዩ ሥራዎች በመሠራት ላይ ይገኛል፡፡ ለዚህም ይረዳ ዘንድ በርካታ የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራሞችና ሕጎች ወጥተዋል፡፡ ይህን አደንቃለሁ፡፡ የዚህ ጽሑፌ ዓላማ ግን ባለፉት 25 ዓመታት ከመሻሻል ይልቅ እየባሰበት የሄደውን ሲቪል ሰርቪሱን የአንድ ድርጅት ካድሬ መዋቅር የማድረግ ሥራ በተመለከተ ያለኝን ሐሳብ ለማስፈር ነው፡፡

ውድ አንባቢያን በየትኛውም አገር ያለ ሲቪል ሰርቪስ በሕዝቡና በሕዝቡ ቀጥተኛ ተወካዮች አማካይነት የብዙኃኑን ይሁንታ አግኝተው የወጡትን ፖሊሲዎች የማስፈጸም ተልዕኮ ነው ያለው፡፡ በእርግጥ የወጡትን ፖሊሲዎች ለማስፈጸም በጥልቀት ከማወቅ ባሻገር በፖሊሲዎቹ ላይ ሲቪል ሰርቫንቱ ጠንካራ እምነት ቢኖረውና ቢያምንባቸው ለአፈጻጸም ምቹ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ሲቪል ሰርቪሱ እምነት ባይኖረውም እንኳ ባለው አቅም ሁሉ ለማስፈጸም መረባረብ የውዴታ ግዴታው ነው፡፡ ሲቪል ሰርቪሱ ፖሊሲዎችን በብቃት ለመፈጸም ብቃትና የተስተካከለ አመለካከት እስካለው ድረስ፣ የየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል በመሆኑ ወይም ከፖለቲካ ነፃ ነኝ ማንንም አልደግፍም ካለ የእኔ አባል ካልሆንክ ብቻ ተብሎ እንግልት፣ አድልኦና ጭቆና ሊደርስበት አይገባም፡፡ በእርግጥ በርካታ አገሮች የሲቪል ሰርቪስ መዋቅራቸውን የፖለቲካ ድርጅት ከመሆን የሚከለክሉ ሲሆን፣ በእኛ አገር ግን ይህ ክልከላ በሕግ ደረጃ ባይኖርም በተግባር ግን ቢገባህም ባይገባህም ኢሕአዴግን በመደገፍ ለሁሉም ነገር ከማጨብጨብ ውጪ ውልፍት ማለትና የተለየ ሐሳብ ማቅረብ የሚያመጣው ቅጣት ከባድ ነው፡፡

እንደ ሌሎች አገሮች በአገራችንም መንግሥት በመንግሥትነቱ መሥራት ያለበት የመረጠውንና ያልመረጠውን ሕዝብ በፍትሐዊነት ማገልገልና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ማገልገል የሚያስችል እምነትና አመለካከት ያለው ሲቪል ሰርቪስ መፍጠር እንጂ፣ ከቀበሌ እስከ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች ድረስ የገዥው ፓርቲ አባላትን ለመመልመል መሆን የለበትም፡፡ አይደለም በአንድ አገር ውስጥ በሚኖሩ ዜጎች መካከል በአንድ ቤተሰብ መካከል በሁሉም ነገር ተመሳሳይ አመለካከት ያለው ሰው ሊኖር አይችልም፡፡ ምክንያቱም ሰዎች ተመሳሳይ ወይም ከአንድ ፋብሪካ የተመረቱ ዕቃዎች አይደሉምና፡፡ በዚች አገር የሚኖር የትኛውም ዜጋ ፍላጎቱና ምኞቱ አገሩ አድጋና በልፅጋ ማየት ነው፡፡ ምኞቱን ተግባራዊ የሚያደርግበት መንገድ ግን የተለያየ ሊሆን ይችላል፡፡ ስለሆነም ሁሉም ሐሳቦች የመደመጥ ዕድል አግኝተው የሰዎች ሳይሆን የሐሳብ ፉክክርና አሸናፊነት ኖሮ ለአሸናፊው ሐሳብ ሁሉም በጋራ መሥራት አለበት እንጂ፣ ከእኔ ሐሳብ ውጪ ሌሎች ሐሳቦች መደመጥ የለባቸውም የሚል ኢ-ዴሞክራሲያዊ አመለካከት ካዳበርን አሸናፊ ሐሳቦችን እየገደልንና ‹‹አድርባይነትን›› እያበረታታን ነው ማለት ነው፡፡  የአባላት ምልመላ ሥራ የፖለቲካ ድርጅቶች እንጂ የመንግሥት አይደለም፣ ሊሆንም አይገባውም፡፡ አሁን በአገራችን ያለው መንግሥት ግን የፖለቲካ ድርጅት  የሚሠራውን ሥራ የሚሠራ፣ ደጋፊዎችን (አባላትን) ለፓርቲ የሚመለምል፣ አባል ያልሆኑትን ከመንግሥት መዋቅር እየመነጠረ የሚያወጣ፣ ሲቪል ሰርቫንቱን በፖለቲካዊ አመለካከታቸው የሚያስቀምጥበት፣ የእኔ አባል ያልሆነ ሁሉ ተቃዋሚ ነው በማለት ድራሹን ለማጥፋት የሚሠራ ነው፡፡

በአንቀጽ 38 እና በሌሎች በርካታ የኢፌዲሪ የሕገ መንግሥት ድንጋጌዎች መሠረት ሁሉም የአገሪቱ ዜጎች በፖለቲካዊ አመለካከታቸው ልዩነት እንደማይደረግባቸው ተገልጿል፡፡ ሆኖም ግን ኢሕአዴግ በሕገ መንግሥቱ እንደነገረን ሳይሆን በአገሪቱ  ሁለት ዓይነት ዜጎች ፈጥሮ እያሳየን ነው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ‹‹አይነኬዎች›› ወይም የድርጅት አባላት ሲሆኑ ሌለኞቹ ደግሞ ‹‹ተረፈ ዜጋዎች›› ወይም የድርጅት አባል ያልሆነው ነን፡፡ ከታች ከቀበሌ አንስቶ እስከ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች ድረስ የገዥው ፓርቲ አባል አለመሆን በወንጀል ያስቀጣል ተብሎ የታወጀ እስኪመስል ድረስ፣ መንግሥት የመንግሥትነት ሥራውን ትቶ ሁሉም ሲቪል ሰርቫንት ከቅጥር ፎርም ጋር በግዴታ የድርጅት ፎርም በማስሞላትና አባላትን በማጋበስ ላይ ተሰማርቶ ይገኛል፡፡ እኔ የፖለቲካ ድርጅት አባል መሆንም ሆነ ፖለቲካ ውስጥ መሳተፍ አልፈልግም ያለ ሲቪል ሰርቫንት አንተ ደጋፊ ካልሆንክ ተቃዋሚ ነህ ተብሎ ተፈርጆ ጫና ይደረግበታል፣ ይዋከባል፣ ክትትል ይደረግበታል፣ ጀርባው ይጠና፣ የአመለካከት ችግር አለበት፣ ፀረ ልማት፣ ተላላኪ፣ የድሮ ሥርዓት ናፋቂ፣ ጠባብ፣ ትምክህተኛ፣ ወዘተ. የሚል ታርጋ ተለጥፎበት በፍርኃት የድርጅት አባል እንዲሆን አለዚያም አንዱ ከሳሽ አንዱ መስካሪ ሆኖ በእነሱ ቋንቋ ‹‹እንዲመታ›› ወይም መሥሪያ ቤቱን እንዲለቅ ይደረጋል፡፡

እንኳን ፖለቲካ ነገር ውስጥ መግባት አልፈልግም ያለ ሲቪል ሰርቫንት ቀርቶ ሥራውን በአግባቡ እስከሠራ ድረስ የተቀዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባልስ ቢሆን ጥፋቱ ምንድነው? ሲቪል ሰርቫንቱ አሁን ላይ የመጣበት ብሔር እየተጠቀሰ አማራ ከሆነ ትምክህተኛ፣ የድሮ ሥርዓት ናፋቂ፣ የግንቦት 7 እና የሰማያዊ ፓርቲ ተላላኪ፤ ኦሮሞ ከሆነ ጠባብ፣ ፀረ አንድነት፣ ገንጣይ አስገንጣይ፣ የኦነግና የመድረክ ተላላኪ፤ ትግሬ ከሆነ የሻዕቢያ ቅጥረኛ፣ የአረና ጆሮ ጠቢ፣ ወዘተ የሚል ስያሜ ተሰጥቶት እዚህ አካባቢ መወለዱን እስኪጠላ ድረስ ነው የሚሰቃየው፡፡ የደረጃ ዕድገት፣ የትምህርት ዕድል፣ አጫጭር ሥልጠናዎች፣ ሽልማቶች ሲመጡ ቅድሚያ ለድርጅት አባላት ነው እየተባለ ምንም የማይሠሩ የድርጅት አባላት ሲሾሙ፣ ሲሸለሙ፣ ሲያድጉ፣ ሲማሩ ለፍቶ የሚሠራ የድርጅት አባል ባለመሆኑ ብቻ እንዲንገላታ፣ እንዲታሰር፣ ከሥራ ተባሮ ያለሥራ እንዲቀመጥ፣ ብሎም በሕገወጥ መንገድ እንዲሰደድ ይደረጋል፡፡ ይኼ ነው በፖለቲካዊ አመለካከታቸው ልዩነት አይደረግባቸውም ማለት?!! በፖለቲካዊ አመለካከታቸው እየተባለ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችን አቅምና ብቃት በሌላቸው የድርጅት አባላት መሙላት ነው እኩልነት?!

በቅርቡ በአንድ መገናኛ ብዙኃን የሚሠራ ጓደኛዬ የድርጅት አባል በመሆኑ በሁለት ዓመት ውስጥ የሠራው ሁለት ፕሮግራም ብቻ ነው፡፡ ግን በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ሁለት ጊዜ ኮከብ ሠራተኛ ተብሎ ተመርጦ ከመሸለሙም ባሻገር ሹመት ተሰጠው፡፡ ምክንያቱም የድርጅት አባል ነዋ፡፡ አሁን በምሠራበት መሥሪያ ቤት ውስጥ ለረጅም ጊዜ ያገለገለና በ2007 ዓ.ም. ከድርጅት አባልነት በቃኝ ብሎ ወጥቶ ጀርባው ይጠና እየተባለ የሚዋከብ አንድ የሥራ ባልደረባዬ የአገር ውስጥ የትምህርት ዕድል ተጻጽፎ ያገኛል፡፡ እናም በመመርያው መሠረት እንዲያስተናግዱት ሲጠይቅ መሥሪያ ቤታችን የድርጅት አባል ያልሆኑ ሰዎችን አቅም እያጎለበተ ለድርጅታችን ጠላት የምናፈራበት አይደለም፡፡ የድርጅት አባል ያልሆነን ሰው አቅም የማጎልበት፣ የማሳደግና የማስተማር ኃላፊነት የለብንም በማለት ያገኘውን የትምህርት ዕድል እንዲያጣ ተደረገ፡፡ ነገር ግን እዚሁ አዲስ አበባ ውስጥ ነዋሪውን አማራችኋል፣ አቅም የላችሁም፣ የትምህርት ደረጃችሁ ዝቅተኛ ነው የተባሉ የወረዳ፣ የክፍለ ከተማና የከተማ የአመራር አካላት በሕዝብ ሀብትና ንብረት በአመራርነት ያገኙት የነበረውን ደመወዝ እያገኙ የትምህርት ወጪያቸው ተሸፍኖላቸው የድርጅት አባል በመሆናቸው በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና የትምህርት ተቋማት ገብተው እንዲማሩ እየተደረገ ነው፡፡ ይኼ ነው እንግዲህ ኢሕአዴግ በዜጎች መካከል ፈጥሬዋለሁ የሚለው እኩልነት??!!

ጥሩ ደመወዝ ለማግኘትና ሥራ ለመቀጠር የድርጅት አባል መሆን ግድ እየሆነ ነው፡፡ የትምህርት ተቋማት ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ነፃ ናቸው እየተባለ ገዥው ፓርቲ ግን በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይመለምላል፣ ይሰበስባል፡፡ በተጨማሪም የድርጅት አባላት የሆኑና ተማሪዎችን የሚመለምሉት የተማሪዎች ዲን አባል እንዲሆኑ እየተደረገ የማስተርስ ትምህርት ይሰጣቸዋል፡፡ ቀሪዎቹ ደግሞ በያዙት የድርጅት ወረቀት አማካይነት ያለ ውድድር እንዲመደቡ ይደረጋል፡፡ በዚህም በዩኒቨርሲቲዎች አካባቢ በትምህርት ጥሩ ግሬድ ከማምጣት ይልቅ በድርጅት “A”፣ “B”፣ “C” ማምጣት ይመረጣል፡፡ በቅርቡ በየክፍለ ከተማው እየተቋቋመ ላለው ‹‹መንገድ ትራንስፖርት ጽሕፈት ቤት›› ሠራተኛ እየተቀጠረ ያለው በድርጅት አባልነት ነው፡፡ በየወረዳው ካሉ በማኔጅመንት ተመርቀው ስድስት ዓመት ያገለገሉ፣ የድርጅት አባል ሆነው በድርጅት ግምገማ “A” ያላቸው ሁለት ሰዎች እየተመለመሉ በስምንት ሺሕ ብር እየተቀጠሩ ነው፡፡ ለዚህም በክፍላተ ከተሞች እየተመለመሉና እየተመደቡ (እየተቀጠሩ አላልኩም) ያሉ ሰዎችን ማየትና ማጣራት አልያም …..ሕንፃ ሄዶ ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ የተመለመሉ ሰዎችን ስም ዝርዝር ማውጣት ይቻላል፡፡ እነዚህ ሰዎች ሰሞኑን ኦረንቴሽን ተሰጥቷቸው ወደ ሥልጠና ገብተዋል፡፡ ከየወረዳው ማደግ ካለባቸው እንኳ ሁሉም ስድስት ዓመት ያገለገሉ የማኔጅመንት ምሩቆች ተመዘግበው እንዲወዳደሩ ማድረግ ይገባ ነበር፡፡ እኔ የማይገባኝ ነገር የድርጅት አባል ያልሆነ ሲቪል ሰርቫንት የሚሠራው ለማን ነው? የሚያገለግለውስ የየትኛውን አገር፣ ዜጋና መንግሥት ነው? ከተቻለ ለዚህ መልስ የሚሰጠኝ አካል ቢኖር ደስ ይለኛል፡፡ በድርጅት አባልነት ብቻ አቅምና ብቃት የሌላቸውን ሰዎች በመቅጠር የመንግሥትን መዋቅር ወደ ድርጅት መዋቅር የመቀየር ሥራ እየተሠራ ለመሆኑ በቂ ማሳያ ነው፡፡

ምንም ሥራ ሳይሠሩ ለመኖር በፈለገው ሥርዓት ለመውጣትና ለመግባት የድርጅት አባል መሆን ግድ ይላል፡፡ የድርጅት አባል ያልሆነ ሰው ሁለት ሴኮንድ እንኳ ቢያረፍድ የሚደርስበት ዘለፋና ቅጣት የትየለሌ ነው፡፡ ታሞ ቢቀርና የሐኪም ማስረጃ ቢያመጣ እንኳ ተቀባይነቱ እጅግ አነስተኛ ነው፡፡ እንዴት ትታመማለህ፣ አውቀህ ሥራ ለመበደል ወይም ወሬ ለማቀበል ነው እንጂ እየተባለ ከተፈጥሮ ጋር እንዲታገል ይደረጋል፡፡ የድርጅት አባል የሆነ ሰው ግን በፈለገው ሰዓት ቢገባ፣ በፈለገው ሰዓት ቢወጣ፣ አንድ ወር ሆነ ሁለት ወር ከሥራ ገበታው ላይ ጠፍቶ ከርሞ ቢመጣ ‹‹የድርጅት ጉዳይ ስለነበረብኝ ነው›› ወይም ‹‹የድርጅት ሥራ ላይ ነበርኩ›› ብሎ መናገር ብቻ ይበቃዋል፡፡ በዓመቱ መጨረሻ ላይ ደግሞ ይኼው ሠራተኛ ‹‹ኮከብ ሠራተኛ›› ተብሎ ይሸለማል፡፡ የድርጅት ሥራን በብቃት የሚሠራ በዚያ ላይ ኮከብ ሠራተኛ ስለሆነ ተብሎ ይሾማል፣ የደረጃ ዕድገት ይሰጠዋል፣ እንዲሁም ትምህርት እንዲማር ይደረጋል፡፡ ሰሞኑን ደግሞ በጣም የገረመኝ ነገር ‹‹አዲሱን የሥራ ምዘናና የደረጃ አወሳሰን›› በተመለከተ ለድርጅት አባላት ብቻ ሥልጠና ተሰጥቶ ለምን ለድርጅት አባላት ብቻ? የሚመለከተው ሁሉንም ሲቪል ሰርቪስ ስለሆነ እኛም ሠልጥነን ግንዛቤው ሊኖረን ይገባል ብለን ሁለት ሰዎች ስንጠይቅ፣ የድርጅት አባል ላልሆኑ ሰዎች አቅም አንገነባም አለን፡፡ ይኼው ሰውዬ መድረክ ላይ ወጥቶ ስለመልካም አስተዳደር፣ ስለፍትሕ፣ ስለዴሞክራሲ ሲያወራ ይሰማል፡፡ አስቂኝ እኮ ነው፡፡ ለነገሩ ከላይ ወርዶላቸው ሊሆን ይችል ይሆናል፡፡

በአጠቃላይ ለአብነት ከዚህ በላይ የጠቀስኳቸውን አነሳሁ እንጂ በድርጅት አባል በሆኑና ባልሆኑ ሰዎች መካከል ያለው ልዩነት ከልጅና ከእንጀራ ልጅ ዓይነትም በላይ ነው፡፡ ስለሆነም ከላይ ያሉት ገዥዎቻችን ይኼን ችግር የማታውቁ ከሆነ በሕግ አምላክ እንለምናችሁ ከዛሬ ጀምሮ ታች ድረስ ፍተሻ አካሂዱ፡፡ የሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴርም በየዓመቱ ትርጉም የሌለውን ‹‹የሲቪል ሰርቪስ ቀን›› ከማክበር በዘለለ ታች ድረስ ወርዶ ክትትል በማድረግ የድርጅት አባል ባልሆኑ ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን ወከባ ለማቃለል ትኩረት ሰጥቶ ይሥራ!!! ከወሬ ይልቅ ተግባር ይቅደም እያልኩ በተዋቂው ፈላስፋ ‹‹በጆን ስቲዋርት ሚል (John Stewart Mill)” ጽሑፌን ላብቃ፡፡

‹‹ከአንድ ሰው በስተቀር የሰው ዘር በሞላ አንድ ዓይነት አስተያየት ቢይዝና ያ ሰው ብቻ ተቃራኒ አስተያየት ቢያዳብር፣ ያ ሰው ማኅበረሰቡን ፀጥ ማሰኘቱ ተገቢ የማይሆነውን ያህል ማኅበረሰቡ ያንን ሰው ፀጥ ቢያሰኘው አግባብነት የለውም፡፡ … አንድን አስተያየት ፀጥ የማሰኘት (እንዳይገለጽ የመከልከል) ልዩ ክፋት የሰው ዘርን በሞላ ያለውንም የሚመጣውንም (የማወቅን ዕድል) መዝረፍ መሆኑ ነው፡፡ … ለመለጎም የምንጣጣራው አስተያየት ስህተት ለመሆኑ ማረጋገጫ የለም፡፡ ማረጋገጫ ቢኖርም እንኳ ለመለጎም መሞከሩ እኩይ ተግባር ነው፡፡ በባለሥልጣናት ሊታፈን የሚሞክረው አስተያየት እንዲያውም ልክ ሊሆን ይችላል፡፡ ሊያፍኑት የሚጥሩት በእርግጥ እውነቱን ይክዳሉ፡፡ ግን እነሱ ስህተት የማይገኝባቸው ፍፁማን አይደሉም፡፡ ለሰው ዘር በሞላ ውሳኔ የማሳለፍና ሌላውን ሰው አይቶ ሰምቶ የመፍረድ ዕድሉን የመንፈግ ሥልጣን የላቸውም፡፡››

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው akalegudatgnawe@gmail.comማግኘት ይቻላል፡፡ 

 

Standard (Image)

ሕዝብ በሚወደውና በሚያከብረው መንግሥት ከመመራት የበለጠ ምን ያስደስተዋል?

$
0
0

በሳሙኤል ረጋሳ

የሰው ልጅ በባህሪው የሚፈልጋቸው ቁሳዊና ህሊናዊ ግብዓቶች አሉት፡፡ ከገንዘብና ከንብረት ጋር የተያያዙ ሊለኩ የሚችሉ አስፈላጊና ከአስፈላጊ በላይ የሆኑ ቁሳዊ ግብዓቶች አንዱ ነው፡፡ ሌላው ፍላጐቱ ደግሞ በስኬት ይኼን ያህል ነው የማይባል ነገር ግን መለኪያቸው ከእርካታና ከመንፈስ ደስታ ወይም ከተስፋ መቁረጥና ከብስጭት ጋር የተያያዘው በዋናነት የመወደድ፣ የመከበርና የመፈራት በውስጡ መኖር ወይም ያለመኖር ናቸው፡፡

በሁለተኛ ደረጃ ላይ የተጠቀሱት ሦስት ነገሮች በግለሰብ፣ በቡድን፣ ወይም በመንግሥት ደረጃ ያላቸው ቦታ ከማንነት ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት አላቸው፡፡ ለጊዜው እነዚህን ጉዳዮች ከመንግሥት ጋር አያይዘን እንያቸው፡፡

መወደድ

አንድ መንግሥት የመወደድ ዕድልን የሚያገኘው ለሕዝቡ በሚያበረክተው ቀንና አገልግሎትና የሕዝቡን ችግር ነቅሶ በማውጣት እንደ ሁኔታው ጊዜያዊም ሆነ ዘላቂ መፍትሔ ሲሰጠውና ሲተገብረው ነው፡፡ ሕዝብ እንዳይጉላላ የተቀላጠፈ አሠራርን ማስቀመጥና በተቻለው የመጨረሻ ፍጥነት ችግር ፈቺ ሆኖ ሲገኝ ነው፡፡ ሕዝቡ ከመንግሥት ጋር ባለው ግንኙነት በሄደበት መሥሪያ ቤት ሁሉ ፈጣን አገልግሎትና ምላሽ አግኝቶ ከረካ፣ መንግሥት በሕዝብ ልቦና ውስጥ የተደላደለ ሥፍራ ይኖረዋል፡፡ መንግሥት ሕዝብን በእኩል ዓይን ካየ፣ ጤናው እንዲጠበቅ፣ እንዲማርና እንዲሠለጥን ካደረገው የራሱን የፍቅር መንገድ ስላበጀ ይወደዳል፡፡ መንግሥት በሕዝብ ሲወደድ ደግሞ ትርጉሙ ብዙ ነው፡፡  

መከበር

መንግሥት የሚከበረው መዋቅሩን በሚመሩት አካላት ሞራላዊ ቁመና ልክ ነው፡፡ እነዚህ መዋቅሮች በመጀመሪያ ብቃት ባላቸው ሰዎች መሞላት አለባቸው፡፡ ብቃት ሲባል የትምህርት ደረጃ ብቻ ሳይሆን በተፈጥሮ ያለው የአመራር ብቃት፣ በልምድ ያዳበረው ክህሎት፣ በሕዝብ ዘንድ ያለው ተቀባይነትና ፍቅር፣ የሥራ ተነሳሽነቱ፣ ውሎው፣ ከሥራ ባልደረቦቹ ጋር ያለው ጤናማ ግንኙነቶች ዋናዎቹ ናቸው፡፡ ለእነዚህ አካላት ከማንኛውም ሙስና ጋር ትንሽም ቢሆን ንክኪ የሌላቸው መሆን አለባቸው፡፡ በተጨማሪም የበላይና የበታች ሠራተኛነት በሚፈቅደው ሕግ መሠረት የማዘዝና የመታዘዝ፣ የመፈጸምና የማስፈጸም ግዴታ አለባቸው፡፡ መንግሥት እንዲከበር መዋቅሩን የሚዘውሩት አካላት የሚፈጸሙት ሁሉ ይኼን ማሟላት አለባቸው፡፡

መፈራት

መንግሥት በሚመራው ሕዝብ ዘንድ መፈራት አለበት፡፡ መፈራት ሲባል ኃይልን በመጠቀም ቅስም የመስበር፣ ያለሕግ የማሰርና የመፍታት ጉዳይና እጅ የማስነሳት አይደለም፡፡ ይኼ አሉታዊ ፍራቻ ነው፡፡ አንድ መንግሥት መፈራት ያለበት የሚያወጣው ሕግ ሕዝቡን ምን ያህል ከጥቃት ይከላከላል? ምን ዓይነት ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጠቀሜታ አላቸው? ብሎ በአገሩ ተጨባጭ ሁኔታ ሊተገበር የሚችል ሕግ ሲያወጣና ሲተገብረው ነው፡፡

ሕጉን ማውጣት የመጀመሪያው ጉዳይ ሆኖ ዋናው ጉዳይ ግን ሕጉ እንዴት ይፈጸማል ነው፡፡ በርካታ አገሮች ጥሩ ሕግ ሊያወጡ ይችላሉ፡፡ ያወጡትን ሕግ የማስፈጸም አቅም ያላቸው ግን ጥቂቶች ናቸው፡፡ ሕጉ መከበር አለበት ብቻ ሳይሆን መፈራትም አለበት፡፡ ሕግን መጣስ በገንዘብና በእስር ከማስቀጣቱም በላይ እስከ ሞት ቅጣት ሊያደርስ ይችላል፡፡ ስለሆነም በትክክል የሚተገብር ሕግ ያስፈራል፡፡ በአገራችን ማንም ሰው አንድን ጥፋተኛ ‹‹በሕግ አምላክ›› ብሎ በማስቆም ያለንክኪና ያለሦስተኛ ወገን ጣልቃ ገብነት ለሕግ ማቅረብ የሚችልበት የቅርብ ጊዜ ትዝታ አለን፡፡ ይኼ ሕግ መፈራቱን በትክክል ያሳያል፡፡ ሕግ የሚፈራው በሁሉም ላይ እኩል ተፈጻሚ ሲሆን ነው፡፡

ብዙ መንግሥታት ግን መፈራት የሚፈልጉት በሕግ ሳይሆን ሕገወጥ በሆነ ዲክታተራዊ አገዛዝ ነው፡፡ ዲክታተሮች አሉታዊ በሆነ መንገድ በኃይልና በጉልበት በማስፈራራት ሕዝቡን በጦር መሣሪያ ሰጥ ለጥ አድርገው ለመግዛትና ለመፈራት ይፈልጋሉ፡፡ እነዚህ መንግሥታት ከመወደድ ይልቅ መከበርን፣ ከመከበር ይልቅ መፈራትን ይመርጣሉ፡፡ ሩቅ ሳንሄድ ከአገራችን ደርግን፣ ከጐረቤታችን ሻዕቢያን መጥቀስ እንችላለን፡፡ የዚህ ዓይነት መንግሥታት መጨረሻቸው አገርንም ራስንም ማጥፋት በመሆኑ መፈራትን በጉልበት ሳይሆን በሕግ ማግኘት አለባቸው፡፡

ከላይ የጠቀስናቸው ሦስት ባህሪያት አዎንታዊ መልሳቸው ሕዝብን ከመንግሥት የሚያዋህዱ ከመሆናቸውም በላይ የአገር ፍቅር ስሜትን በዋናነት የሚፈጥሩ ናቸው፡፡ ሕዝቡ ለአገር ዳር ድንበር መስዋዕት እንዲሆን፣ በተጨማሪም የመንግሥትን ከማንኛውም ጥቃትና አደጋ መጠበቅን እንደ ዋና መርህ ይቀበላቸዋል፡፡

አግባብነት የሌለው ተቃውሞ ማንሳትና ማስነሳት፣ ለጠላት መሣሪያ መሆን፣ በተቻለ ሁሉ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ቀውስ መፍጠር፣ አገር ጥሎ መሰደድ ብሎም እስከ አጥፍቶ መጥፋት የሚያደርሰው መነሻው ምንም ይሁን ምን መንግሥትን ከመጥላት፣ ካለማክበርና ከፍርኃት ነው፡፡

አብዛኛዎቹ የአፍሪካ መንግሥታት የሚወደዱ አይደሉም፡፡ ምክንያቱም ሕዝቡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የመረጣቸው አይደሉም፡፡ ባለሥልጣኖቻቸው የሕዝብን ጥቅም ከማስከበር ይልቅ የራሳቸውንና የባለሟሎቻቸውን ጥቅም ለማሟላት የሚጥሩ ናቸው፡፡ በሥልጣናቸው ይባልጋሉ፡፡ ወገናቸውን ብቻ ለመሾምና ለመጥቀም የተቀመጡ ናቸው፡፡ በሕይወት ዘመናቸው ተጠቅመውበት ሊጨርሱት የማይችሉትና በዘላቂነት የእነሱ መሆኑን እርግጠኛ ያልሆኑበትን ንብረት በሕገወጥ መንገድ ይሰበስባሉ፡፡ በመሆኑም እነዚህ የመንግሥት ሹመኞች በሕዝብ ዘንድ አይወደዱም፣ አይከበሩም፣ አይፈሩም፡፡ ድምር ውጤቱ ግን የመንግሥትን ያለመፈለግ የሚያመላክት ነው፡፡ እጅግ የሚበዛው ቦታ ላይ የሚመደቡት ሰዎች ከሌሎች የተሻለ ብቃት ኖሮአቸው አይደለም፡፡ ይልቁንም ከበላዮቻቸው ጋር ባላቸው የጥቅም ትስስር ወይም ለፖለቲካው ታማኝ ሳይሆኑም ቢሆን በመምሰል የሚሾሙ ናቸው፡፡ እነሱ በሚፈጽሙት ወራዳ ተግባር ሕዝቡ ለመንግሥት ተገቢውን ከበሬታ አይሰጥም፡፡

ሕዝብ መንግሥትን የማይወድ፣ የማያከብርና የማይፈራ ከሆነ መብቶች ሁሉ በጉልበተኞችና በጉበኞች እጅ ገብተዋል ማለት ነው፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥ መኖር ደግሞ ከክፉ ነገር ሁሉ የከፋ ክፉ ነገር ነው፡፡

እንደ አፍሪካ ባሉ ታዳጊ አገሮች በመንግሥት ደረጃ የመወደድ፣ የመከበርና የመፈራት ዕድል ማግኘት በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ በበርካቶች ዘንድ መንግሥት ሕዝብን ማስተዳደር ያለበት ሁሉን በእጁ ሁሉን በደጁ የማድረግ ሥልጣንን የተቀባ ነው የሚል አስተሳሰብ አለ፡፡ መሪዎቹም በአገሪቱ ሀብት የማዘዝ፣ እነሱ ለሚፈልጉት ዓላማ ጦርን ማሰማራት፣ ሕዝቡን በግዴታ ወይም በውዴታ ግዴታ ማዘዝን የመሳሰሉ ሥልጣኖች ሁሉ የእኔ ናቸው ባዮች ናቸው፡፡ ሕገ መንግሥትንና ሌሎች ሕጐችን መጀመሪያ የሚጥሱት ባለሥልጣናት ስለሆኑ ሌላው ሕዝብ የሚፈራው ሕግም ሆነ መንግሥት የለም፡፡

እነዚህ እውነታዎች በብዙ የአፍሪካ አገሮች የታዩ ሲሆን፣ እኛም በመጠኑም ቢሆን የምንጋራቸው ነገሮች ስለሚኖሩ ከፍተኛ አመራሮቻችን ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው ቁጥጥራቸውን ያጠናክሩ፡፡

እስቲ ከአገራችን ሁኔታ ጥቂት ማሳያዎችን ወስደን እንይ፡፡ ከወራት በፊት ኦሮሚያ ውስጥ የተነሳው ብጥብጥ መንስዔው የክልሉ መስተዳድር በሚያደርሰው የመልካም አስተዳደር ዕጦትና በአግባቡ ሕዝብን መምራት ያለመቻሉና ሌሎችም ተጨማሪ ጉድለቶች እንደሆኑ በመንግሥት ደረጃ ተገልጿል፡፡ በዚህ ሁከት ምክንያት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አልቀዋል፡፡

ታዲያ አጥፊው በመንግሥት ደረጃ በታወቀበት በሕግ አግባብ የተወሰደ ዕርምጃ ሕዝቡ የሚያውቀው የለም፡፡ የሕዝብን ቀልብ ለመሳብ ሁለት ባለሥልጣት የሥራ መደብ ለውጥ አድርገዋል፡፡ ይህንን ያየ ሕዝብ ለወደፊቱ በክልሉ መንግሥት ላይ እንዴት እምነት ሊኖረው ይችላል? እውነት የዚያ ሁሉ ጥፋት ማጠንጠኛ እነዚህ ሰዎች ናቸው? ለወደመው ንብረትና ለሞቱ ሰዎች ምክንያትስ ሆኖ ሊቀርብ ይችላል? ይኼ ጉዳይ ዘላቂ የሆነ ሰላምን ሊያሰፍን በሚችል ሁኔታ ስላልተጠቃለለ ወደፊት ተመሳሳይ ችግር ላለመፈጠሩ ምን ማረጋገጫ አለ? ችግሩ ሄዶ ሄዶ ተንገራግጮ ስለቆመ መንግሥት ‹‹ሾላ በድፍን›› ብሎ ያለፈው ይመስላል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር ያዘጋጀው ብሔራዊ ፈተና ከመሥሪያ ቤቱ ሾልኮ በመውጣቱ ከፍተኛ የሆነ ሁለንተናዊ ቀውስ አስከትሏል፡፡ የሚገርመው ፈተናው ከነመልሱ በፌስቡክ ተለቆ አገር ሁሉ ካወቀው በኋላ የትምህርት ሚኒስትሩ ጉዳዩ ሐሰት ነው ሲሉ አስተባብለዋል፡፡ በማግሥቱ የፈተናው ሰዓት ደርሶ ሲጀመር የእኛ አይደለም ያሉት ፈተና የራሳቸው ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ስለዚህም ፈተናው እንዲመክን ተደረገ፡፡ በአንድ ራስ ሁለት ምላስ ከየት መጣ? ፈተናውን ያወጣው ትምህርት ሚኒስቴር ነው፡፡ በፌስቡክ ተለቆ ፈተናውን ያየው ትምህርት ሚኒስቴር ነው፡፡ ፈተናው የእኛ አይደለም ያለው ትምህርት ሚኒስቴር ነው፡፡ በማግሥቱ ፈተናው የእኛ ነው ያለውም ያው ትምህርት ሚኒስቴር ነው፡፡

ይኼ ፍቺ ያልተገኘለት እንቆቅልሽ ነው፡፡ ለዚህ ጥፋትና ብክነት እንዲሁም ለተማሪና ለወላጆች ሞራል ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም፡፡ መንግሥትም ምንም ነገር እንዳልተፈጠረ ሾላ በድፍን ብሎ ነገሩን አልፎታል፡፡

ከዚህ ክስተት በኋላ ተመሳሳይ የብሔራዊ ፈተና ሥርቆት ግብፅ ውስጥ ተፈጽሟል፡፡ እንደኛው ሁሉ ጥያቄውና መልሱ በድረ ገጾች ተለቋል፡፡ ታዲያ የግብፅ መንግሥት ጣጣ ሳያበዛ የፈተናውን መሰረቅ አምኖ ዕርምጃ ወስዷል፡፡ አጥፊ ያላቸውን ሁሉ በቁጥጥር ሥር አውሏል፡፡

መጋቢት 25 ቀን 2008 ዓ.ም. በወጣው ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ አንድ ጽሑፍ ወጥቷል፡፡ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢንቨስተሮች በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣ ጨረታ ተካፍለው አዲስ አበባ ላይ ሙሉ ክፍያ ከፍለው በሕጋዊ መንገድ ቤት ገዝተዋል፡፡ ይኼ በፍርድ አፈጻጸም በኩል ዕውቅና አግኝቶ ሳለ የተረከቡትን ይዞታ ክፍለ ከተማው አይገባችሁም ብሎ ቤቱን አፍርሶባቸዋል፡፡ ባለጉዳዮች ለተለያዩ አካላት ቀርበው ጉዳያቸውን ቢያመለክቱ ሰሚ ስላጡ ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት ፍርድ ቤት ከሰው መብታቸውን ለማስከበር ሞክረዋል፡፡ ፍርድ ቤትም ለባለመብቶቹ ሲወስን ጉዳዩ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤትም ቀርቦ ፀንቷል፡፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ክፍለ ከተማው ውሳኔውን ሊቀበል አልቻለም፡፡ የሚገርመው ነገር ውሳኔውን ያለመቀበል አንድ ነገር ሆኖ ያልተቀበለበትን ምክንያት የክፍለ ከተማው ሥራ አስፈጻሚ ሲገልጹ፣ ‹‹ባለጉዳዮች ምንም ጥፋት የለባቸውም፡፡ ሁሉን ነገር የፈጸሙት ሕጉን ተከትለው ነው፤›› ብለው፣ ችግሩን የፈጠረውና ያላግባብ የወሰነው ፍርድ ቤት መሆኑን፣ ስለዚህ በእነሱ በኩል መርምረው የመንግሥትን ጥቅም አለመንካቱን ሳያረጋግጡ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ተቀብለው መሬቱን እንደማያስተላልፉ ገልጸዋል፡፡

የቦሌ ክፍለ ከተማ ሥራ አስፈጻሚ የከለከሉት መብት

  1. ባለጉዳዮቹ በሕጋዊ አግባብ ቤቱን የገዙት በመሆናቸው ጥፋት እንደሌለባቸው ገልጸው ነው፡፡
  2. ችግሩን የፈጠረውና ያላግባብ የወሰነው ፍርድ ቤት መሆኑን ገልጸው ነው፡፡
  3. ጉዳዩ በሕግ የተያዘ መሆኑን ጠቁመው የመንግሥትን ጥቅም አለመንካቱን ሳያረጋግጡ መሬቱን ማስተላለፍ እንደማይችሉ ገልጸዋል፡፡

እንግዲህ በሕግ አግባብ በመንግሥት አዋጅና ደንብ መሠረት የተሸጠን ቤት ያለማስረከባቸው አንዱ ጉዳይ ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ የፍርድ ቤትን ውሳኔ አልቀበልም ማለት ትልቅ ጥፋት ነው፡፡ እንዲሁም የፍርድ ቤትን ውሳኔ በይግባኝ ሳያሽሩ ፍርድ ቤት ጥፋተኛ ነው ማለት ጠያቂ ቢኖር መዘዙ ብዙ ነው፡፡ ለመሆኑ ክፍለ ከተማው ማን ሆነና ከፍርድ ቤት በላይ የመንግሥትን ጥቅም የማስከበር ይግባኝ ሰሚ የሆነው? ፍርድ ቤቶች የመንግሥትን ጥቅም አያስከብሩም ማለት ነው?

ግለሰቦች ተነስተው ሕገ መንግሥቱ የደነገገውን የፍርድ ቤት ነፃነት በአደባባይ ሲጥሱ አንድም የመንግሥት አካል የማስተካከያ ዕርምጃ መውሰድ አልቻለም፣ ወይም አልታየም፡፡ አስፈጻሚው ቢቀር ፓርላማው ያወጣውን ሕግና በሕዝብ የፀደቀው ሕገ መንግሥት እንደ ተራ ነገር ሲገፋ የርስ በርስ ሚዛናዊ ቁጥጥር (Check and Balance) የለም ማለት ነው? ምንም ጉዳዩ ቀላል የግለሰቦች ጉዳይ ቢመስልም የሕገ መንግሥቱን ምሰሶ የሚያነቃንቅ በመሆኑ ሕግ አውጭውም ሆነ አስፈጻሚው ትኩረት ሊሰጡት ይገባል፡፡

አንድ ክፍለ ከተማ ደፍሮ የፍርድ ቤትን ውሳኔ የማይቀበል ከሆነ ሕዝቡ በመንግሥትና በሕግ አምኖ መኖር አይቻለውም፡፡ ስለዚህ ሰዎች የሚፈራ ሕግ ስለሌለ እነሱም ሕጉን አይፈሩም፡፡ መንግሥት ደግሞ ሕግን ካላስከበረ አይፈራም፡፡

ከላይ የተነሱት ጭብጦች በከተማ አስተዳደር፣ በክልልና በፌዴራል ደረጃ ለሚታዩ የመንግሥት ህፀፆች ማጣቀሻ ናቸው፡፡ እነዚህ ችግሮች አይፈጠሩም አይባልም፡፡ ለምን ተፈጠሩም አይባልም፡፡ መባል ያለበት መንግሥት ጉዳዮቹን እንዴት ያያቸዋል ነው፡፡ መንግሥት የሚፈጠሩትን ስህተቶች በተቻለ ሁሉ ማረም አለበት፡፡ በሁሉም እርከን ያሉ የመንግሥት አካላት እንደነዚህ ያሉ ጉልህ ስህተቶች ሲፈጽሙ መጨረሻው ምን ይሆናል?

አንድ ጋን በአንድ በኩል ሰበራ ሆኖ ውኃውን የሚያፈስ ከሆነና በሌላው በኩል ሁሉ ደህና ቢሆን፣ በተሰበረው በኩል ብቻ ያፍስስ ሌላው አካሉ ደህና ማለት አያዋጣም፡፡ መንግሥትም ችግር ሲፈጠር በጐ ጐን ብቻ አስቦ በሾላ በድፍን መንፈስ ማስተካከያ ያለመውሰድ ትልቅ አደጋ አለበት፡፡

በእርግጥ መንግሥት የመወደድና የመከበር ብሎም የመፈራትን መርህ ሊያሟሉለት የሚችሉ ብቁ መደላድሎች ፈጥሯል፡፡ የሕዝቡን አቤቱታና ቅሬታ ማስተናገድ የሚችሉ ዴሞክራሲያዊ ተቋማት ገንብቷል፡፡ በመርህ ደረጃ የሚከተለው አቋምም ደህና ነው፡፡ ነገር ግን ትግበራዎቹ ወደተፈለገው ግብ እንዳይመሩ በፌዴራል፣ በክልልና በከተማ አስተዳደሮች ደረጃ የሚቀሩት ከበርካታ በላይ ጉዳዮች አሉ፡፡ ችግሮችን ከመሠረቱ ለመፍታት መንግሥት ለምን ቁርጠኛ እንዳልሆነ ግራ የሚያጋባ ነው፡፡ በእርግጥ መንግሥት መወደድ፣ መከበርና መፈራት ያለበት በአገሪቱ ውስጥ ባሉ በሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች አይሆንም፡፡ በአመፀኞች፣ በሕገወጦችና የግል ጥቅምን ከሚያሳድዱ ግለሰቦችና የፖለቲካ ድርጅቶች ይኼንን መጠበቅ አይገባም፡፡ እንደ ሕዝብ ግን ሌላው ቀርቶ በጥቂቱም ቢሆን እነዚህን ጉዳዮች ያለሟሟላት የመንግሥትን አቋም የተወለካከፈና ለወደፊት አብሮ የመቀጠል ጉዳይን ጥያቄ ውስጥ ያስገባል፡፡ ለመሆኑ መንግሥታችን በዚህ በኩል ራሱን ገምግሞ ያለበትን ደረጃ ያውቃል? አንድ ሕዝብ በሚወደው፣ በሚያከብረውና በሚፈራው መንግሥት ከመመራት የበለጠ ምን ያስደስተዋል?

   ከአዘጋጁ፡-ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

 

Standard (Image)

በውስጣዊ ችግሮች የተተበተበችው ኢትዮጵያ አረንጓዴ ካርድና ኤርትራ

$
0
0

ባለፈው ወር የተባበሩት መንግሥት ድርጅት ተወካዮች በኒውዮርክ ባካሄዱት ስብሰባ ለኢትዮጵያ አንድ ለየት ያለ ውሳኔ ማሳለፉቸው ይታወቃል፡፡ ይህም ኢትዮጵያ ተለዋጭ የፀጥታው ምክር ቤት አባል አገር አድርጐ የሹመት ደብዳቤ በመስጠት የሁለት ዓመት አባልነቷን አረጋግጧል፡፡ አንድ መቶ ሃያ ሰባት አገሮች ድምፅ ቢሰጧት አባል የመሆን ዕድል የነበራት ኢትዮጵያ፣ የአንድ መቶ ሰማኒያ አምስት አገሮችን ድምፅ ተችራ የምድራችንን ፖለቲካዊ ሁኔታ ይወሰናል ተብሎ በሚገመተው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆናለች፡፡ እ.ኤ.አ. በ1959 እና በ1981 አባል የነበረች አገር በአሁኑ ወቅት ደግሞ ለሦስተኛ ጊዜ ዕድሉን አግኝታለች፡፡

ዕድሉን ለምን አገኘች? የሚል ጥያቄ ብናነሳ መልሱ ሊሆን የሚችለው ኢትዮጵያ ከቀጣናዊ ሚናዋ ባሻገር በአኅጉራዊና በዓለም አቀፍ ደረጃ ለዓለም ሕዝብ ሰላምና ፀጥታ መስፈን በተጫወተችው ሚና፣ የተሰጣት አረንጓዴ ካርድ ነው የሚል ምላሽ ልናገኝ እንችላለን፡፡

ይህች አገር እንደ አገር ከተቆረቆረችበት ከ3,000 ዓመታት ጀምሮ የነበራት ኃያልነትና ተሰሚነት ከፍ ያለ እንደነበር ከታሪክ እንረዳለን፡፡ ዕድለኛው ደቡብ ዓረቢያ ተብሎ ይጠራ የነበረውን ግዛት ከማስተዳደር ጀምሮ በወራሪው ጣሊያን ላይ ያሳየችው የጀግንነትና የበላይነት ተጋድሎ ተፍቆ የማይጠፋና ብል የማይበላው የታሪክ አካሏ ነው፡፡ ይህ ታሪክ ደግሞ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የዓለም ታሪክ ሆኖ ሲታወስ እንደሚኖር ጸሐፍትና ባለሙያዎች ብዕራቸውን አንስተው በነጭ ወረቀታቸው ላይ አስፍረውት ይገኛሉ፡፡ ለአብነት ያህል ባርትንስኪ ማኬል የተባሉ የእንግሊዝ የታሪክ ተመራማሪ፣ ‹‹የግዮን ወንዝ መፍለቂያ የሆነችና በምሥራቅ አፍሪካ የምትገኝ አንድ ኃያል አገር አለች፡፡ ስሟም ኢትዮጵያ ይባላል፤›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡ እንደ ባርትንስኪ ገለጻ ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ የውኃ ማማ (The Water Tower of East Africa) ብቻም ሳትሆን ኃያሏና ስመ ገናናዋ አገር ተብላ ትጠራ እንደነበር እንረዳለን፡፡

እንግዲህ ኢትዮጵያ ይህን የመሰለና የተከሸነ ታሪክ ባለቤት መሆኗ የዓለም ምሁራንና ባለሙያዎች በየብዕሮቻቸውና ሚዲያዎቻቸው ሲጽፉ ማንበብና ሲናገሩ መስማት አዲስ ጉዳይ አይደለም፡፡ ይህ ጉዳይ ብርቅ ባልሆነበት አገር ውስጥ ተለዋጭ የፀጥታው ምክር ቤት አባል ሆኖ መሾም ምን ይደንቃል የሚል አስተያየት ሊቀርብ ይችላል፡፡ ይህ አስተያየት እውነታነትና ተቀባይነት ያለው ጉዳይ እንደሆነ እንረዳለን፡፡ የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን የምሥረታ ቻርተር ከማርቀቅ አንስቶ እስከ ተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ምሥረታ ድረስ ከፍተኛ ሚና የነበራት አገር፣ ዛሬ በስንት ዓመት አንዴ ያውም አብዛኛዎቹ የአኅጉሮቹ አገሮች ዕድል እንዲያገኙ ተደርጐ በሚሰላው ሒሳብና በሚሰጠው ድምፅ አገራችን ዕድሉን ማግኘቷ አዲስ ጉዳይ እንዳልሆነ፣ እንዲያውም ከዚህ የተሻለ ኃላፊነት ብትታጭ እንኳ የሚያንሳት መሆኑን መረዳት እንችላለን፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ አገሪቱ በአሁኑ ወቅት ያለችበት ነባራዊ ሁኔታስ ምን ይመስላል? የሚል ጥያቄ ብናነሳ ገና ውስጣዊ ችግሮቿ ፊቷ ላይ አፍጥጠው ያሉባት አገር በመሆኗ ለራሷ ቅድሚያ ብትሰጥ የሚል አስተያየት አስፍረን እናልፋለን፡፡

ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በጅማሮ ላይና ይበል የሚያሰኙ መሠረተ ልማቶች ላይ ብትሆንም፣ በተቃራኒው ደግሞ የአገሪቱን ኢኮኖሚና የቆየ ታሪክ ጥላሸት የሚቀቡ ድርጊቶች እየተከናወኑባት ነው፡፡ ከእነዚህ መካከል በመልካም አስተዳደር ዕጦት እየተከሰቱ ያሉ ኢ-ፍትሐዊ አሠራሮችና ሙስና ዋነኛ ጉዳዮች ናቸው፡፡ ለአብነት ያህል ሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ይፋ ባደረገው ሪፖርት አንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እንኳ ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ በሕገወጥ መንገድ ግለሰቦች እጅ እንደገባ ይፋ አድርጓል፡፡ ይህ የብዙ ሺሕ ኢትዮጵያውያንን ድህነትና ረሃብ ሊቀርፍ የሚችል ገንዘብ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡ በዚህም የተነሳ በአሁኑ ወቅት በአገራችን በተለይም በአዲስ አበባ የሙስናና የኢ-ፍትሐዊ አሠራር ደረጃዎችና ውስብስብነታቸው ከፍ እያለ እንደመጣ እንረዳለን፡፡

ሌላው ጉዳይ ደግሞ በኢኮኖሚያዊ ችግር የተነሳ እየተስፋፋ የመጣው ስደትና የጐዳና ተዳዳሪነት ጉዳይ ነው፡፡ የዓለምን ሕዝብ ችግር ለመፍታት የተሰየመችው አገር የራሷን ችግር ለመፍታት ስትቸገር ስናይ ለመረዳትና ምን ብለን ማለፍ እንዳለብን እንቸገራለን፡፡

ሦስተኛ ችግር ተደርጐ ሊወሰድ የሚችለው ጉዳይ ደግሞ ከገጠር ወደ ከተማ ያለው ፍልሰት ነው፡፡ ይህንን ጉዳይ መንግሥት ብዙ ትኩረት እንዳልሰጠው ብንረዳም፣ በአገሪቱ በተለይም በከተሞች የኑሮ ውድነት ላይ እያደረሰ ያለው አሉታዊ ተፅዕኖ ከባድ ሆኗል፡፡ ይህ ጉዳይ በከተሞች በተለይም በአዲስ አበባ ውስጥ የመኖሪያ ቤት ዕጦትና ሌሎች ማኅበራዊ ቀውሶች እያስከተለ እንደሆነ ግልጽ ጉዳይ ነው፡፡

ከአገሪቱ ውስጣዊ ችግሮች አለፍ ስንል ደግሞ ኤርትራን እናገኛለን፡፡ ወንድምና እህት የሆነው የኢትዮጵያና የኤርትራ ሕዝብ በኤርትራው ገዥ መንግሥት ፖለቲካዊ አቋም የተነሳ ሁለቱ ሕዝቦች ተራርቀዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር አስመራ ላይ የከተመው የኢሳያስ አፈወርቂ መንግሥት የሚፈትል የሚቋጥረው ጉዳይ ቢኖር ኢትዮጵያን የማተራመስ አጀንዳ ቀርፆ መንቀሳቀስ ነው፡፡ በኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወንጀለኛና አሸባሪ ተብለው የተፈረጁትን ቡድኖች ወታደራዊ ሎጅስቲክስ ከማሟላት ባሻገር ሥልጠና በመስጠትና በማስታጠቅ ኢትዮጵያ እንደ ሶሪያና ሌሎች የአሸባሪዎች መናኸሪያ እንደሆኑት አገሮች ለማድረግ ሌት ከቀን እየሠራ መሆኑ የዘወትር ድርጊቱ ገላጮች ናቸው፡፡

በእነ ጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ ብርቱ ትግል በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውሳኔ በኢትዮጵያና በኤርትራ እ.ኤ.አ በ1952 ተመሥርቶ በ1962 ዓ.ም የፈረሰውን ፌዴሬሽን ተከትሎ፣ የተከፉ ኤርትራውያን የተወሰኑ የዓረብ አገሮችን ድጋፍ አገኙ፡፡ በዚህም የተነሳ እነዚህ አገሮች ኤርትራ ዓረባዊ ናት መገንጠልና የራሷን እስላማዊ መንግሥት ማቋቋም አለባት በማለት እ.ኤ.አ በ1961 ‹‹ተጋድሎ ሓርነት ኤርትራ›› ወይም በዓረብኛ አጠራሩ ‹‹ጅብሃት ታህሪረል ኤሪትሪያ (ጀብሃ)›› የተባለ ቡድን እንዳቋቋሙ ታሪክ ይናገራል፡፡ እንግዲህ ይህ ቡድን እርስ በራሱ ሲጨፋጨፍ ኑሮ ነው በመጨረሻ ‹‹ሕዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ (ሻዕቢያ)›› በሚል ኃይል የተተካው፡፡ ሻዕቢያም በተወሰኑ የሙስሊም ዓረብ አገሮች ዛሬ በዘሩት ልክ እያጨዱ ያሉትን ኢራቅና ሶሪያን ጨምሮ ትጥቅና ስንቅ በገፍ እየቀረቡለት ኤርትራን የመገንጠል ህልም እውን ያደረገው፡፡

ዛሬ አስመራ ላይ ከትሞ የገዛ ወገኑን ለባህር አዞና ለበረሃ ሰለባ እያደረገ ያለው የኤርትራው አምባገነን መንግሥት ኢትዮጵያን የአገሮች ሁሉ ጭራ የማድረግ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ለተለዋጭ የፀጥታው ምክር ቤት የሰጣትን አረንጓዴ ካርድ ጥላሸት ለመቀባትና ካርዱ እንዳይሠራ የማድረግ አባዜውን አጧጡፎ የነበረው፡፡ 

ስለዚህ በአሁኑ ወቅት ኤርትራና በዙሪያዋ ያሉ አሸባሪዎች የኢትዮጵያን ህልውና እስከ ማፈራረስ የሚደርስ አጀንዳ ቀርፀው እየተንቀሳቀሱ ያሉ ቡድኖች በመሆናቸው፣ የአገራችን መንግሥት በውጭ ፖሊሲ ግንኙነት ላይና በዓለም ላይ ተሰሚነትንና ዝናን ለማትረፍ ደፋ ቀና ከሚል፣ በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ቢሠራ የተሻለ እንደሚሆን አስተያየቴን ማስቀመጥ እፈልጋለሁ፡፡

ውስጣዊ ችግሮች ለውጫዊ ችግሮች በር የሚከፍቱ ጉዳዮች በመሆናቸው በአሁኑ ወቅት የአገራችን መንግሥት እዚህም እዚያም እየታዩ ያሉ ውስጣዊ ችግሮች ላይ ትኩረት ማድረግ አለበት፡፡ ለእያንዳንዱ ችግር ተገቢው ምላሽ መሰጠት አለበት፡፡ የችግር ከባድና ቀላል ስለሌለው እዚህም እዚያም እየታዩ ላሉ ችግሮች አፋጣኝ መልስ መስጠት ይገባል፡፡ በየቴሌቪዥኑና ጋዜጣው የአገራችንን ዕድገትና ከየትኛው አገር ጋር የንግድና ሌሎች ተያያዥ ስምምነቶችን መፈራረማችንን የማስተጋባት አባዜ ወጥተን በትክክልና የሕዝባችንን ችግር ሊፈታ በሚቻል ጉዳይ ላይ ትኩረት ማድረግ አለብን፡፡

የሚነሱ ዴሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብቶች በተገቢ ሁኔታ ምላሽ ማግኘት አለባቸው፡፡ ተለዋጭ የፀጥታው ምክር ቤት አባል አገር ሆነን የዓለምን ችግርና ኢ-ፍትሐዊ አሠራር እንታገላለን እያልን ወደ ውጭ ከማሰብ አባዜ ወጥተን፣ እየተሠሩ ያሉ ኢ-ፍትሐዊና ኢ-ዴሞክራሲያዊ አሠራሮችን በቁርጠኝነት መታገልና ማስወገድ አለብን፡፡ የችግሮቹን ምንጭና መንስዔ ከሥሩ በመለየት መፍትሔ መስጠት ይገባል፡፡ ያኔ ለውጫዊ ኃይሎች ተጋላጭ አንሆንም፡፡ ውጫዊ ኃይሎችም ቢሆኑ መግቢያ ቀዳዳ አያገኙም፡፡ ቢገቡ እንኳ ሕዝቡ ራሱ ያጋልጣቸዋል፡፡ ያኔ ለፀጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ብንሆን ተሰሚነታችንና ተፅዕኖ ፈጣሪነታችን ከፍተኛ ይሆናል፡፡ ኤርትራም ካርዳችንን ወደ ቢጫነትና ቀይነት የመቀየር አቅምም ተቀባይነትም አይኖራትም፡፡

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው zemelove@gamil.comማግኘት ይቻላል፡፡          

 

 

,

 

Standard (Image)

በኢቢሲ ላይ የቀረበው ትረካ የማይታመን ነው

$
0
0

በዕውቀቱ ሲንጅ

ደራሲ ከበደ ሚካኤል ባሳተሙት ታሪክና ምሳሌ መጽሐፍ ‹‹በዓለም ላይ ትልቅ ሥራ ለመሥራት የሚቻለው ሠሪው ሰውና ለመሥራት የተመቸበት ጊዜ እነዚህ ሁለቱ ሲገናኙ ነው፡፡ ትልቁን ሥራ ለመሥራት የሚቻለው ሰው ባልተመቸ ጊዜ ሲፈጠር ሊሠራው የሚችለውን ሥራ ሳይሠራው መቅረት ግድ ይሆንበታል፡፡ ልሥራም ቢል ጊዜው አይደለምና አይሆንለትም፡፡ ትልቁ ሥራ ለመሥራት የተመቸ በሆነበት ጊዜ ደግሞ ሊሠራው የሚችል ሰው ባለመፈጠሩ መልካሙ ጊዜ በከንቱ ያልፋል፡፡ እነዚህ ሁለቱ ተፈላላጊ ነገሮች የሚገናኙት በብዙ ዘመን ጥቂት ጊዜ ነው፤›› ብለዋል፡፡

አንባቢያን ሐምሌ 20 ቀን 2008 ዓ.ም. በሪፖርተር ጋዜጣ ልናገር በሚለው ዓምድ ሥር ‹‹የኢቢሲ ግዞተኞች›› የሚል መጣጥፍ እንዳነበባችሁ ታሳቢ በማድረግ፣ ከመነሻው እስከ መድረሻ በጽሑፉ ይዘትና በጸሐፊው ’አብዮት’ በቀረቡ ትችቶችና ትዝታዎች ያየነውን ብዥታ ከንፈር ከመምጠጥ ባሻገር በተቻለ ለማጥራት በማለም፣ የሚከተለውን አጭር አስተያየት ለማቅረብ በማሰብ እንዲህ ተዘጋጀ፡፡

ጸሐፊው በኢቢሲ ያለፉትን ሁለት ዓመታት በሦስት ዘመናት በመከፋፈል ትዝታቸውን ሲያካፍሉን፣ በመጀመሪያው ዘመን በአመራሩ የተደረገው እንቅስቃሴ ሥር ነቀል ለውጥ ነበር ወይ? ለሚለው አይደለም ያሉ ወገኖች ለለውጡ እንደ አደናቃፊ ታይተው በአመራሩ የታዩበትን አግባብ፣ በአመራሩ መካከል የድርጅቱ አካሄድ ትክክል አይደለም ባሉ የሐሳብ መከፋፈል በመፈጠሩና ወደ ሠራተኛው በመውረዱ ቡድንተኝነት መፈጠሩን፣ አምባገነናዊነት መንገሡንና የመሳሰለውን ጠቅሰዋል፡፡ አመራሩ የሚዲያ ዕውቀት እንደሚያንሰው፣ አንዳንዶቹን የቀድሞ አመራር ተልዕኮ የተሰጣቸው ናቸው በአግባቡ አልረዱኝም በሚል በአመራሩ ጀማሪነት የፖለቲካ ሽኩቻ መፈጠሩን፣ በሥልጣን ላይ ያለው የራሱን ቡድን በመመሥረት ሌላውን ማዳከም መሆኑን፣ በአመራሩ መሀል የሐሳብ ልዩነት መስፋት የተሰናባቹ አመራር መብዛት፣ የስፖርት ዶክመንተሪ ሥራ ኃላፊዎች መልቀቃቸውን አትርሱ ብለውናል፡፡ አንዳንዶቹ አመራሮች የሐሳብ ልዩነቱን ይበልጥ በማስፋት አስተያየት በመስጠታቸው የፈሩት ላይቀር ከኃላፊነት ቦታ መነሳታቸውን፣ ኢቢሲ 50ኛ ዓመት በዓሉን የራሱን አመራር ዘመን ብቻ ማወደሱ ተወቅሶ፣ ሕዝቡን ከጊዜያዊ ስቱዲዮ እያለ ከጅማና ከድሬዳዋ የሚያስተላልፈው በዲኤስኤንጂ መሣሪያ በመጠቀም እንጂ ከጊዜያዊ ስቱዲዮ ስላይደለ ኢቢሲ ሕዝብ ማታለሉን፣ የሬዲዮ ጋዜጠኞች በግዞት ወደ ዘነበወርቅ መላካቸው ትኩረት አለመሰጠቱን በጠቅላላው የመልካም አስተዳደር ልሳን ነኝ እያለ የመልካም አስተዳደር ችግር ያለበት፣ ዴሞክራሲ የሌለበት ሚዲያ ሆኖ በመዝለቁ መንግሥት ውሳኔ ይስጥበት ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ለዴሞክራሲ ግንባታ ወሳኝ ድርሻ ካላቸው ተቋማት የመንግሥት ሚዲያ አንዱ ነው፡፡ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ተግባራዊ የሚሆነውም በሚዲያ መድረኮች ነው፡፡ ሚዲያው ነፃነቱን ጠብቆ እንዲስፋፋና እንዲዳብር ማድረግ ዋነኛ የመንግሥት አቅጣጫ ሲሆን፣ ይህንኑ ተቋም ለማጠናከርና በነፃነትና በጤናማ አኳኋን እንዲያድግ ለመደገፍ ከፍተኛ ርብርብ መደረጉና መንግሥት ለዋና ዋና ሥራዎች ከሚሰጠው ትኩረት የማይተናነስ ትኩረት በመስጠቱ ሊመሰገን ይገባዋል፡፡ ሚዲያው ለኪራይ መሰብሰብ ዓላማ እንዳይውልና የኪራይ ሰብሳቢዎች መፈንጫ እንዳይሆን የሚያስፈልጉ ኢኮኖሚያዊ ዕርምጃዎችን መንግሥት የወሰደው ዘግይቶ በቅርቡ ነው፡፡ ጤነኛ የመንግሥት ሚዲያ ተቋማትን በተለየ ሁኔታ በመደገፍ የሕግ የበላይነትን በጥብቅ እንዲያከብሩ ዋነኛ የመፍትሔ አቅጣጫዎች ተደርገው መወሰዳቸው ሌላው በጎ ጎን ነው፡፡

አንባቢያን እንደሚያውቁት የኪራይ ሰብሳቢነት መገለጫ ፀረ ዴሞክራሲያዊ የጠባብነትና የትምክህተኝነት አመለካከቶች አንዱ ሲሆን፣ የመንግሥትን ሥልጣን ተቆጣጥሮ ይህንኑ እንደማትነጥፍ ጥገት እያለቡ መክበር ነው፡፡ ጠባቦችና ትምክህተኞች የሚያነሷቸው ጉዳዮች በሙሉ የመንግሥትን ሥልጣን ተጠቅሞ ኪራይ መሰብሰብ የሚመለከቱ ናቸው፡፡ አንዱ ትልቁ መፈክራቸው የመንግሥት ቦታዎች ለእኛ ብሔር ተወላጆች አልተሰጡም ስለሆነም ተጠቃሚ አልሆንም ነው፡፡ የየብሔሩ ጥገኛ በመንግሥታዊ የኃላፊነት ቦታዎች የሚደለደል ቢሆን ካበረከተው አስተዋጽኦ በላይና ከዚሁ ደመወዝ ውጪ እየተከፈለው የሚጠቀም ሲሆን፣ በዚሁ ላይ የሕዝብ ንብረት መዝረፍ፣ በአካባቢው ያለውን ተቆጣጥሮ ሌላ ብሔር ሳይጋራው ብቻውን መዝረፍ ላይ ከገባ የሚያገኘው የኪራይ ሰብሳቢነት ጥቅም ቀላል እንደማይሆን ይገመታል፡፡ ኪራይ ሰብሳቢነት ሊናድ የሚችለው በሰዎች ነው፡፡ ሰዎች ደግሞ ሥራቸውን የሚሠሩት እንዲሁ በደመ ነፍስ ሳይሆን አንዳች አመለካከት ይዘው በአመለካከቱ በመመራት ነው፡፡ የሕግ ልዕልና በጥብቅ እንዲከበር በማድረግ ኪራይ ሰብሳቢነትን መናድ ይቻላል፡፡

የሕግ የበላይነት መሠረታዊ የሕግ መርሆ ነው፡፡ ሕዝብ በተስማማባቸው ሕጎች አጥር ውስጥ ታጥሮ መሥራት ጉልበተኛውም ደከም ያለውም መብትና ጥቅሙን የማስጠበቅ አኩል ዕድል እንዲያገኝ የሚያደርግ መሣሪያ ነው፡፡ ሕግ የማያከብረው ጥቂትና አልፎ አልፎ የሚከሰት ነገር እንዲሆን፣ ሲከሰትም የሚያስቀጣና የሚታረም ነገር እንዲሆን ማድረግ የመልካም አስተዳደር አንዱ መርሆ ነው፡፡

ጸሐፊው ‹‹አብዮት›› በጽሑፋቸው እንዳስቀመጡት በአመራር ደረጃ የነበሩ ከሥራቸው የመልቀቅ ሚስጥር ከፍ ሲል እንደገለጽኩት ግለሰቦቹ ካበረከቱት አስተዋጽኦ በላይ አካባቢያቸውን ተቆጣጥረው ሌላው ሳይጋራቸው ለመዝረፍ የሚያስችለው ቀዳዳ ስለተደፈነባቸው ነው የሚል ሐሳብ አለኝ፡፡ ‘ሁለት እግር አለኝ ተብሎ ሁለት ዛፍ ላይ እንደማይወጣ’ እያወቁ በኢቢሲ በሥልጣን እርካብ ላይ ያሉቱ ያለ ፈቃድ ደግሞ ተመሳሳይ የግላቸውን ሥራ ሲያከናውኑ ሲደረስባቸው ‘ግመል ሰርቆ አጎንብሶ’ እንደሚባለው ሆነው ከሁለት አንዱን እንዲመርጡ ተጠይቀው በፈቃዳቸው በመልቀቃቸው ነው፡፡ ሁሉንም አንጋፋ ጋዜጠኞች እናከብራለን ሲለዩንም እናዝናለን፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ በአዲሱ አመራር ድጋፍና ትብበር ሲጠየቁ ኩራት ስለተሰማቸው በያዙት ቱባ ደመወዝ የሚመጥናቸው ቦታ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ሌሎቹም ቢሆን ኢቢሲን ሳይሆን አገር ከድተው ኮብልለው ወደ አውሮፓ መሄዳቸው ድብቅ አይደለም፡፡ በኢቢሲ መንደር የፈጠረው ጸሐፊው እንደሚሉት ድንጋጤ ሳይሆን አግራሞት ነው፡፡ አመራሩ ሰውን ከተግባሩና ከአመለካከቱ እንጂ እንደ ጨው ቀምሶ የሚለይበት መሣሪያ የለውም፡፡

ስለሆነም እንደ ቀድሞው አሠራር እንደ ልብ መገላበጥ ያልቻሉቱ ጥቂቶቹ በራሳቸው ፈቃድ ለቀዋል፡፡ የዶክመንተሪ ሥራ ክፍልና ስፖርት ክፍል ጋዜጠኞች በተመሳሳይ የሚታይ ነው፡፡ የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ መለያቸው 'ከአምስት እስከ ስድስት'የሚል ቅጽል በሠራተኛው የተሰጣቸው አመራር ሥራ የሚገቡና የሚወጡበት ሰዓት ለማመልከት ሲሆን፣ በእርግጥም ተረጋግጧል፡፡ እኝሁ ሴት ከነበሩበት የተነሱት ቀደም ሲል በተለያየ ጊዜ በስብሰባ በሰጡት አስተያየት መነሻ ሳይሆን፣ ከያዙት ሥራ መደብ  ይልቅ ሙሉ ጊዜያቸውን ለኢቢሲ አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ በሚችሉበት በሙያቸው በሌላ ሥራ ለመመደብ በማስፈለጉ ነው፡፡

አሁን አሁን በወቅቱ ያልታዩ በርካታ የቀድሞ አመራር የአሠራር ግድፈቶች ዘግይተውም ቢሆን እየሰማን ሲሆን፣ ከአሁኑ ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ የባለሙያ ፍልሰት የሚስተዋልበት ጊዜ ነበር፡፡ በሚዲያ እንደተነገረው ኢሬቴድ በፕሮጀክት ሥራዎች የማስፋፋት ሥራው ከፍተኛ ብክነት የተስዋለበት ዘመን ሲሆን፣ ድርጅቱ የሚያሠራጫቸው ፕሮግራሞችም በሕዝቡ ዘንድ በአግባቡ በጥራት ባለመድረሱ ዛሬም ድረስ የዘለቀው የሕዝቡ እሮሮ ሳይጠቀስ የሚታለፍ አይደለም፡፡ ኢሬቴድ ተጠሪ በሆነበት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና በሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም፣ በብሮድካስት ባለሥልጣንና በፍርድ ቤት ሳይቀር የተቋሙን ገጽታ የሚያጠቁሩ የግምገማ ውጤቶችና ክሶች የአንባቢያን የቅርብ ጊዜ ትዝታ ናቸው፡፡ በዋናነት ባዕድና የቤት ልጅ በሚል ሠራተኛውን የሚከፋፍል ሥርዓት ስለነበር አብዛኛው ሠራተኛ ለብዙ ጊዜ የተካበተ ችግር፣ ብሶትና ሰቆቃ እንደ ብል የበላው በእጅጉ የተማረረ ስብስብ ነበር ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ በመጨረሻ የቀድሞው ኤሬቴድ (ኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት) የኪራይ ሰብሳቢነት መፈንጫ ለመሆኑ እንደ ጋንግሪን በሽታ በታዩበት የጎሉ ምልክቶች በሚመለከታቸው ሐኪሞች በመረጋገጡ፣ መፍትሔው ሥር ነቀል ለውጥ በመሆኑ አመራሩን በሌላ መተካቱ አስፈላጊ ነበር፡፡

እነዚህን አሉታዊ ዕዳዎች መረከቡን ታሳቢ ያደረገው አዲሱ አመራር ገና ከመነሻው ሚዲያው ከቀድሞው በተሻለ ነፃነት ለማከናወን የሚያስችል ምኅዳር ለመፍጠር ባዕድና ቤተኛ የሌሉበት፣ ለሁሉም ሠራተኛ እኩል የመሳተፍ ዕድል የሚሰጥና እንደየድርሻቸው እንዲያበረክቱ ዕድል የሚሰጥ፣ ሁሉም ባበረከተው አስተዋጽኦ ልክ ከጥቅሙ ተጋሪ የሚሆንበት ስትራቴጂካዊ መካከለኛና የአጭር ጊዜ ዕቅድ በመንደፍ ወደ ሥራ ገብቷል፡፡

በዕቅድ በክንውንና በአፈጻጸምና በግምገማ በየደረጃው ሠራተኛው የተሳተፈበት ሪፖርት በየጊዜው ቦርድ በተገኘበት ለጠቅላላው ሠራተኛው እየቀረበና እየተገመገመ፣ ስኬቱ እየተሞገሰ በድክመቱ ደግሞ እየተተቸ በአብላጫ ስኬታማ ሥራዎች ማስመዝገብ ችሏል ባይ ነኝ፡፡ ይህ ልምድ ባለፉት የቀድሞ አመራሮች ያላየነውና የሠራተኛውን ተስፋ ያለመለመ መልካም ጅምር ሆኖ ታይቷል፡፡ ሌላው ቢቀር ይህ ተግባር ብቻ በራሱ ሥር ነቀል ለውጥ ነበር ለማለት እደፍራለሁ፡፡ በዓለም ከታወቁ ዝነኛ የሚዲያ ተቋማት ልምድ በመቀመር በዓለም አቀፍ ደረጃ በተደረገ ጨረታ ተወዳድረው ባሸነፉ የእንግሊዝ ኩባንያ፣ በኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዕገዛ መዋቅርና የሥራ መደብ ተዘጋጅቶ በማስፀደቅ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡

ስለሆነም ያ የቀድሞው ኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የነበሩበት ብርቱ ችግሮች በቅጡ ተጠንተው ያ ባዕድና ቤተኛ የሚባሉ ሠራተኞች የነበሩት ተቋም ፈርሶ ወደ ኮርፖሬሽን ተሸጋግሯል፡፡ ለዚህ አዲስና ከፍተኛ ኃላፊነት የመሸከም ተቋም የሚመጥን ሙያዊና ትምህርት ብቻ ሳይሆን የተስተካከለ አመለካከት ለውጥ ይፈለግ ነበርና ተገቢው ተደርጓል፡፡ በዚህ ፈጣን ለውጥ ምን ይዞ ይመጣ ይሆን በሚል አንዳንዱ ፍርፋሪ ተቋዳሽ ሠራተኛና ኪራይ ሰብሳቢው ሁሉ በለውጡ ምክንያት ቀድሞ የለመደውን እንዳያጣ መፍራቱ አይደበቅም፡፡ ይህን ለውጥ ሥር-ነቀል አይደለም ብለው እነዚህ ሰዎች በመከራከር የሐሳባቸውን የበላይነት በማሳየት ሌላውን ለማሸማቀቅ ሞክረዋል፡፡ በሰው ልጆች መካከል ሊኖር የሚገባውን የሐሳብና የአመለካከት ልዩነት ከግምት በማግባት እነዚህ ተከራካሪዎችን ወይ በሒደት እንዲረዱትና ለውጡ ለሚፈልገው ሁሉ ተባባሪ እንዲሆኑ፣ ያልተመቸው ደግሞ አማራጩ ከድርጅቱ በራሳቸው ፈቃድ ማግለል እንደሚችሉ በአመራሩ አስተያየት መሰጠቱ ምን ክፋት አለው? ጸሐፊው ‹‹አብነት›› ግን ተሳልቀዋል፡፡ በዋናነት ሊመልሱት የሚገባው እነዚህን እንቅልፍ የነሷቸው ጉዳዮች በጊዜው ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ሌሎች መፍትሔ እንዲፈለግ እንደ ጋዜጠኛ ምን ዕርምጃ ወስደዋል?

በጸሐፊ አብዮት የቀረቡትም ሐሳቦች ስለአዲሱ አመራር አሉታዊ ብቻ በመሰሉ ጉዳዮች በማተኮር ጊዜ ማጥፋታቸው በሥነ ልቦነ ባለሙያዎች አስተያየት ለከፋ ድብርት የመጋለጥ ምልክት ሊሆን ስለሚችል ጥላቻውን የሚለውጡበትን መንገድ እንዲያስቡ ያስፈልጋል ባይ ነኝ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ያነሷቸው ሐሳቦች በንፅፅር ያለመቅረቡና ከስታንዳርድ ምን ያህል ወደፊት ወይ ወደኋላ እንደራቀ ስለማያሳይ ለማወዳደር የሚቸግር ነው፡፡ የሆነውስ ሆነና ጽሑፉን ሲዘጉ ማሳረጊያው አንባቢያንን የዘለፉበት መንገድ አነጋጋሪ ጉዳይ መስሎ ይታየኛል፡፡ ጸሐፊው ’አብዮት ’ጽሑፍዎትን በሪፖርተር ጋዜጣ የሚያነብ ‘ደደብ ነው’ ብለው መደምደሚያ የመስጠትዎ ቅኔው አልገባኝም፡፡

ይልቁንስ አሁን ያለው አመራር መገለጫ በመወያየት ሁሉም በአሸናፊነት ሊወጣ የሚችልበትን ሥልት ነው የተከተለው ብዬ የማስበው፡፡ ችግሮችን ለመፍታት ሰዎችን እንደ አጋር እንጂ እንደ ተቀናቃኝ አልተመለከተም፡፡ ሐሳብ መካፈል፣ አማራጭ ማየት፣ ጥቅምና ጉዳቱን መመዘን እንጂ አቋም ይዞ መከላከልና ተቀናቃኝ ለማጥቃት ጊዜ የነበረው አይመስለኝም፡፡ ሌላውን የሚያዳምጠው ያላያቸውን ሐሳቦች የማየት ዕድል ለማግኘት ነበር፡፡ በአንፃሩ የሠራውን ለማፍረስ ብርቱ ጥረት ተደርጓል፡፡ የስትራቴጂካዊ ዕቅድ ለማውጣት ጨረታ ሲወጣ በሐሰተኛ ክስ ጨረታው በስድስት ወራት እንዲዘገይ በማስድረግ ለጊዜውም ቢሆን ተሳክቶላቸዋል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ አመራር መወቀስ ካለበት ሊወቀስ የሚገባው ከነስ£ሩ በመረጃ የያዛቸውን የቀድሞ አመራሮች በዝምታ ማለፉ ትልቅ ውለታ ውሎ ይሆን? ለነገሩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኪራይ ሰብሳቢነታቸው በኦዲት የተረጋጡትንና ጥፋት ላይ ያገኛቸውን የቀድሞ አመራሮች ለቀድሞ ለበረሃ ትግል ውለታቸው በማሰብ በዝምታ አልፎ የለምን?

ወደ ጉዳያችን ስንመጣ በየትኛውም መሥፈርት ብናየው ከሥራ የለቀቁትም ሆኑ ሌሎቹ ለአዳዲስ ሐሳቦች ዓይናቸውን የዘጉ፣ በክርክር የራሳቸውን የበላይነትና የሌላውን ደካማነት በመፈለግ የሚደክሙ ነበሩ፡፡ ሌላውን የሚያዳምጡት ደካማ ጎኑን በመፈለግ ለማጥቃት ነበር፡፡ በሐሳብ መለየትን የማይደግፉት የተለየውን ሐሳብ ባለማክበር ጭምር ነበር፡፡ ሙያችን ጥበብ ነው በሚል ብሂል ሥራችንን በቼክ ሊስት ለምን አቅዱ ትሉናላችሁ? ለምንስ የምንወጣና የምንገባበትን ጊዜ ቁጥጥር ይደረግብናል? ሰዓት ፊርማ አሻራ አንሰጥም በቼክ ሊስት አናቅድም ማለት ሄዶ ሄዶ የኪራይ ሰብሳቢነት ተግባሮች ናቸው፡፡ ይልቁንስ እንደ መጨረሻ መጨረሻ የለውጥ እንቅስቃሴውን በማያደናቅፍ መንገድ ኪራያቸውን የሚሰበስቡበትን ዘዴ ቢያስቡ ለሌላው ሥራ እንዳይበላሽ በመጠንቀቅ መቻቻል ማለት ይኼ ነው፡፡

እርግጥ ነው የቡድንተኝነት፣ ጠባብነት፣ አምባገነንት፣ የሐሳብ ልዩነቶች ዛሬም ድረስ በጉልህ መዝለቃቸው የሚስተዋሉ ክስተቶች ሲሆን፣ ወደፊት ትግል የሚጠይቁ አጀንዳዎች ናቸው፡፡ ቀደም ሲል እንዳልነው መልካም አስተዳደር የሕግ የበላይነት ምሰሶው ነው ስንል ሕግ የማያከብረው ጥቂትና አልፎ አልፎ የሚከሰት ነገር እንዲሆን፣ ሲከሰትም የሚያስቀጣና የሚታረም ነገር ማድረግ አሁን ያለው አመራር ዓብይ ጉዳይ እንደሚያደርግ ተስፋ ይደረጋል፡፡ ሌላው የኢቢሲ 50ኛ ዓመት የተሳካ ሲሆን፣ ከቀድሞ አመራሮችና ሠራተኞች ፈቃደኛ የሆኑቱ ለዚህ ተብሎ በተቋቋመው ኮሚቴው በማፈላለግ የተገኙቱ ሠራተኞች በእንግድነት ተጠርተው ሽልማት የተሰጣቸው ነበሩ፡፡ የቀድሞ አመራሮች አለመገኘት ምክንያት አይታወቅም፡፡ በዝግጅቱ ግን ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ተገኝቶበታል፡፡

ጸሐፊው የሬዲዮ ዝግጅትና ሥርጭት ሠራተኞቹ ጭምር ወደ ቀድሞው ቦታው ዘነበወርቅ መዛወር እንደ ግዞት በመቁጠር ዋና ርዕስ ማድረጋቸው፣ ኢቢሲ በመልካም አስተዳደር ዕጦት ስቃይ ውስጥ ነው ብለው የመልካም አስተዳደር ልሳን መሆኑ ደግሞ አስገርሟቸው፣ በዚህና በሌሎች ክሶቻቸው መንግሥት ዕርምጃ እንዲወስድ ጠይቀዋል፡፡ እውነታው በሬዲዮ ዜናና ፕሮግራም ዝግጅት የተሰማሩ ባለሙያ ጋዜጠኞች ወደ ቀድሞ ዘነበወርቅ የመሄዱ አስፈላጊነት ላይ ጥናትና ውይይት አድርገው ባቀረቡት የውሳኔ ሐሳብ መሠረት በበላይ አመራር ተወስኖ ነው፡፡ የዚህ ዓላማ የሬዲዮ ጋዜጠኛውን በማግለል ሳይሆን በቀድሞ አመራር ትኩረት ተነፍጎት ወደኋላ የቀረውን ሬዲዮ ጣቢያ ለሥራው ትኩረት በመስጠት እንዲያንሠራራ በማሰብ ነው፡፡ እስከማውቀው የተመደቡት ሠራተኞች በፈቃዳቸው የመረጡት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ መንግሥት ቦርድ ያቋቋመው የተቋሙን ስትራቴጂካዊ ችግሮች ተረድቶ የበኩሉን ለማድረግ ነው፡፡ ከፍ ሲል ያቀረቧቸውን ጉዳዮች ቦርዱ በተለያየ ጊዜ ያያቸው አሉ፣ ሆኖም ለምክር ቤት ቀርቦ በቅሬታ ወይም በትችት የቀረበበትን አናስታውስም፡፡

በአጠቃላይ የኢቢሲ ጉዞ እንደ አንድ ጋራ ፕሮጀክት ግንባታና ዕድገት ጉዞ ልናየው እንችላለን፡፡ አሁን የሚዲያው አባል የሆነው በአንድ ወቅት ታላቁ መሪ እንዳሉት ወደንና የጋራ ፕሮጀክቱ ተዋናይ መሆን አማሎን ነው፡፡ ሁላችንም የፕሮጀክቱ መሥራች አባላት ቤተኞች ነን፡፡ ሬዲዮ ሆነ ቴሌቪዥን በሙሉ ትኩረታችን ውስጥ ያሉ ናቸው፡፡ ከእንግዲህ በተለየ ሁኔታ ቤተኛ ሆኖ ለመቀጠል የሚከጅል ወይም በባይተዋርነት ውጭ ውጭ ማየት የሚከጅል የመኖር አጋጣሚ ውስን ነው፡፡ ሁሉም ለጋራ ፕሮጀክቱ አስተዋጽኦ የማድረግ እኩል ዕድል አለው፡፡ ይህ ሚዲያ ጤናማ ሆኖ የበለጠ ለመጠናከር የመንግሥት ከጎን መሠለፍ የበለጠ ያበረታታናል፡፡

ሕዝቡ እንደ ዋነኛ የመረጃና የፖሊሲ ትንታኔና ክርክር ምንጭ የሚወሰድበት ደረጃ በፍጥነት ይደርሳል፡፡ ፕሮግራሞቹ በጥራታቸው፣ በማራኪነታቸውና በሥነ ምግባር ደንብ አክባሪነታቸው በምሳሌነት የሚጠቀሱ እንዲሆን ተስፋ ይደረጋል፡፡ አለመታደል ሆኖ የአመራሮች ገድል መልካም ሆነው ሳለ አንዳንዶቹ የወደዱትን እንደ መልዓክ፣ የጠሉትን ደግሞ እንደ ጭራቅ ሲያደርጉ የግለሰቦች ሰብዕና በመሀል ቤት ጠፍቶ መልካምም ይሁን እኩይ ሥራው ለቀጣዩ መማሪያ ሳይሆን ማየቱ ያሳዝናል፡፡ መሪና አመራር ግለሰቦች የሚመጡና የሚሄዱ ኃላፊዎች ሲሆኑ በተነፃፃሪ ተቋም ዘላቂ ነው፡፡ ስለዚህ ከመጀመሪያው ሥራና ተግባራችን እንዲያምር ከሆነ የማንንም አስተዋጽኦ የማጣጣልና የማኮሰስ ዓላማ ተገቢ አይደለም፡፡

ከፍ ሲል የዘረዘርኳቸው ጸሐፊ ‹‹አብዮት›› ያቀረቡልን ትዝታዎች እንደተረዳሁት በስማ በለው ያወቁት እንጂ ባላረጋገጡት በርካታ ጉዳዮች እስካሁን እንደ ትውስታ መያዝ ስለማይገባቸው ለጤናቸው ሲሉ ቢረሱት እመክራለሁ፡፡ በአብዛኛው አሉ እያሉ ስለተረኩልን ብዙዎቹ ትረካዎቻቸው ተዓማኒነታቸው አጠራጣሪ በመሆናቸው ከስም ማጥፋት ያልተለየ ውንጀላ መስሎ ይታየኛል፡፡

ከአዘጋጁ፡-ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው sinjh@yahoo.comማግኘት ይቻላል፡፡

 

 

                                                                                                                                                                       

 

Standard (Image)

የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ሕግን አክብረው ከሠሩ የሚዘጉበት ምክንያት አይኖርም

$
0
0

በበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ኤጀንሲ

በአገራችን ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ የበጎ አድራጎት ሥራን በአግባቡ የሚመራ የሕግ ማዕቀፍ አልነበረም፡፡ አዋጅ 621/2001 የበጎ አድራጎት ድርጀቶችና ማኅበራት በአገሪቱ የልማትና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ውስጥ ያላቸውን ሚና ለመደገፍና ለማሳለጥ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ ነው፡፡ ይህ አዋጅ የኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 31 ለዜጎች የሰጠውን የመደራጀት መብት ተግባራዊ እንዲሆን ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ሲሆን ዜጎች ተደራጅተው በአገራቸው የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና የልማት ሥራዎች ላይ ያለምንም ገደብ እንዲሳተፉ ግልጽ በሆነ መልኩ ደንግጓል፡፡

በአዋጅ 621/2001 መሠረት የተቋቋመው የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ኤጀንሲ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት እንዲስፋፉና ተልዕኳቸውን በሕግ መሠረት እንዲወጡ ብሎም ግልፅነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት አሠራር እንዲጎለብት ዓላማ አንግቦ እየሠራ ይገኛል፡፡ ኤጀንሲው ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድረስ በአገሪቱ 3,115 የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ተመዝግበው በሥራ ላይ ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ 416 የውጭ አገር በጎ አድራጎት ድርጀቶች፣ 2,646 በኢትዮጵያ ውስጥ የተደራጁ በጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት እንዲሁም 53 ኅብረቶች ናቸው፡፡

ኤጀንሲው እነዚህ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት አዋጅ 621/2001 በሚፈቅደው መሠረት በሕዝብ ስም ያገኙትን ሀብትና ንብረት በተገቢው መንገድ ሥራ ላይ በማዋል የተቋቋሙለትን ዓላማ ከግብ እንዲያደርጉ በሚያግዝ መልኩ የድጋፍና ክትትል ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ለአብነት ያህል በ2008 በጀት  ዓመት ኤጀንሲው የ2756 በጎ አድራጎት ድርጀቶችና ማኅበራት ፋይል በመመርመር ዓመታዊ ዕቅድ፣ ሪፖርትና የፕሮጀክት ስምምነት ገምግሟል፡፡ ይህንን መነሻ በማድረግ 824 የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ላይ የመስክ ክትትል አድርጓል፡፡ በተደረገው ክትትል ሕግን የተላለፉ 206 የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ የሚደርስ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡

የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ከታዩባቸው ችግሮች መካከል ከተቋቋሙለት ዓላማ ውጪ መንቀሳቀስ፣ ያለኤጀንሲው ፈቃድ የባንክ አካውንት መክፈት፣ የገቢ ምንጫቸውን አለማሳወቅ፣ ዓመታዊ የሥራና የኦዲት ሪፖርት በወቅቱ አለማቅረብ፣ የቋሚ ንብረት ዝርዝር አለማሳወቅ፣ የፕሮጀክት ስምምነት ሳይፈራረሙ መሥራት፣ አስተዳደራዊ ወጪዎችን ከዓላማ ማስፈጸሚያ ወጪዎች ጋር መቀላቀል፣ አስተዳደራዊ ወጪ ከ30 በመቶ በላይ መጠቀም፣ ልማትን ከሃይማኖት ጋር ቀላቅሎ መሥራት፣ ያለፈቃድ የገቢ ማስገኛ ሥራዎች ላይ መሰማራት ለአብነት የሚጠቀሱ ግኝቶች ናቸው፡፡

በ2008 በጀት ዓመት 122 የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ተዘግተዋል፡፡ ከዚህ ውስጥ 119 በጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት በራሳቸው ጥያቄ፣ ፈንድ በማጣትና ለሦስት ዓመታት ምንም እንቅስቃሴ ባለማድረጋቸው የተዘጉ ናቸው፡፡ በተጨማሪም ባክነር አዶፕሽን ኤንድ ማተርኒቲ ሰርቪስ፣ ግሎባል ኢንፋንቲልና ሜዲስን ዱሞንድ የተባሉ ሦስት የውጭ በጎ አድራጎት ድርጅቶች በፈጸሙት የሕግ ጥሰት ማስጠንቀቂያ ቢሰጣቸውም ያሉባቸውን ችግሮች ባለማስተካከላቸው ተዘግተዋል፡፡ አብዛኞቹ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ከጅምሩ አቅም ፈጥረው ወደ ሥራ ያልገቡ በመሆናቸው መዘጋታቸው በአገር ላይ የሚያስከትለው ጉዳት የለም፡፡ የገንዘብ እጥረት ያጋጠማቸው የበጎ አድራጎት ድርጅቶች አዋጁ የፈቀደላቸውን የተለያዩ ገቢ ማስገኛ ሥራዎች ላይ ተሰማርተው ዓላማቸውን ለማስቀጠል ምንም ጥረት አላደረጉም፡፡ በሌላ በኩል በ2008 በጀት ዓመት መሥፈርቱን ያሟሉ 187 የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ተመዝግበዋል፡፡ ለ803 የበጎ አድራጎት ድርጅቶች የፈቃድ እድሳት ተሰጥቷል፡፡

በአዋጅ 621/2001 መሠረት የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ከሚያገኙት ገቢ 70 በመቶ የማያንሰውን ለዓላማ ማስፈጸሚያ (በቀጥታ ለተጠቃሚው የሚደርስ) እንዲሁም 30 በመቶ የማይበልጠውን ለአስተዳደራዊ ወጪ እንዲያውሉት ይደነግጋል፡፡ ሆኖም በርካታ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ይህንን ሕግ ጠብቀው እየሠሩ አይደለም፡፡ ኤጀንሲው የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ሕግን ጠብቀው እንዲሠሩ የተለያዩ የምክክር መድረኮችን በማዘጋጀት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ሠርቷል፡፡ ኤጀንሲው ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ድረስ በዋናነት ትኩረት ሰጥቶ ሲሠራ የቆየው የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት በዘርፉ የወጣውን ሕግ አውቀው እንዲተገብሩ መስመር የማስያዝና የማስተማር ቢሆንም፣ በተሟላ መልኩ ሕግን አክብሮ መሥራት ላይ አሁንም ብዙ የሚቀሩ ሥራዎች አሉ፡፡ ሆኖም ኤጀንሲው የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን መዝጋት እንደ መፍትሔ አይወስድም፡፡ ይሁን እንጂ የበጎ አድራጎት ድርጅቶቹና ማኅበራቱ የሚዘጉት መሥራት የሚችሉባቸው ሁሉም አማራጮች ተፈትሸው መቀጠል የማይችሉ መሆናቸው ሲረጋገጥ ብቻ ነው፡፡

እውነታው ከላይ በዝርዝር ሆኖ እያለ አንዳንድ የአገር ውስጥና የዓለም አቀፍ ሚዲያዎች የጠራ መረጃ ሳይዙ ኤጀንሲው በርካታ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እየዘጋ መሆኑን በስፋት ዘግበዋል፡፡ ለአብነት ያህልም በፍሪደም ሀውስና በዶቼ ቬሌ ሬዲዮ ጣቢያ ኤጀንሲው ከ200 በላይ የበጎ አድራጎት ድርጀቶችን ያላግባብ እንደዘጋ ተደርጎ የተዘገበው መረጃ ከእውነታ የራቀ ነው፡፡ በ2008 በጀት ዓመት በተለያዩ ምክንያቶች የተዘጉ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ቀደም ሲል እንደተጠቀሰው 122 ብቻ ናቸው፡፡ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ሕግን አክብረው እስከሠሩ ድረስ እንዲዘጉ የተደረገበት ሁኔታ የለም፡፡

በተጨማሪም እነዚህ ሚዲያዎች አዋጁ 621/2001 የበጎ አድራጎት ድርጀቶችና ማኅበራት ጉዳዮች ላይ እንዳይሠሩ ገደብ አድርጓል የሚል ሐሳብ በስፋት አንፀባርቀዋል፡፡ ይህ አስተያየት ሕጉን በአግባቡ ካለመረዳት የመነጨ ነው፡፡ በአዋጅ 621/2001 መሠረት የገቢ ምንላቸው ከአሥር በመቶ በላይ ከአገር ውጭ የሚያገኙ በኢትዮጵያ ውስጥ የተቋቋሙ የነዋሪዎችና የውጭ በጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት፣ በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና በዜጎች መብት ነክ ጉዳዮች ላይ መሥራት አይችሉም፡፡ በሌላ በኩል አዋጁ እነዚህ በጎ አድራጎት ድርጅቶች በማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ሥራዎች ላይ እንዲሰማሩ ፈቅዷል፡፡

የገቢ ምንጫቸው 90 በመቶ ከአገር ውስጥ እንዲሁም አሥር በመቶ የማይበልጠውን ከውጭ የሚያገኙ በአገሪቱ ዜጎች የተቋቋሙ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት በልማት፣ በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና በመብት ነክ ጉዳዮች ላይ መሥራት ይችላሉ፡፡ በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሒደት ውስጥ የዜጎች መብትና ጥቅሞች ማስከበር ለኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ብቻ የተሰጡ ናቸው፡፡ አገር በቀል የሙያና ብዙኃን ማኅበራት የሚቋቋሙት ይህን ዓላማ ዕውን ለማድረግ ነው፡፡ የዜጎችን የዴሞክራሲ መብትና ጥቅሞችን ለማስከበር የሚሠራው ሥራ እንደ ልማቱ ትልቅ ሀብት የሚጠይቅ አይደለም፡፡ በመሆኑም በዜጎች ብቻ ሊሠሩ የሚችሉ ናቸው፡፡ በአጠቃላይ ሲታይ አዋጁ ሁሉም የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት በልማት ሥራዎች ውስጥ እኩል ተሳትፎ እንዲኖራቸው ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡ አዋጁ የአገርን ደኅንነትና ጥቅምን በሚያስጠብቅ መልኩ ተቃኝቶ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከምንም በላይ ለሰፊው ሕዝብ ጥብቅና የቆመ ሕግ መሆኑን መረዳት ተገቢ ነው፡፡

ምንም እንኳን ክፍተቶች ቢኖሩም የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት በልማቱ ዘርፍ ላበረከቱት መልካም ሥራ ዕውቅና ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ የኅብረተሰባችንን ችግር በመቅረፍ ረገድ እያደረጉት ያለው አስተዋጽኦ ቀላል የሚባል አይደለም፡፡ ከፍተኛ መጠን ያለው ሀብት በማመንጨት ክፍተት በሚታይባቸው የልማት ሥራዎች ላይ እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ ለአብነት ያህል የኤጀንሲው ዓመታዊ ሪፖርት እንደሚያመለክተው፣ በ2008 በጀት ዓመት 641 የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ብቻ 19,155,771,263 ብር (አሥራ ዘጠኝ ቢሊዮን አንድ መቶ ሐምሳ አምስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሰባ አንድ ሺሕ ሁለት መቶ ስልሳ ሦስት ብር) በጀት ይዘው ወደ ሥራ ገብተዋል፡፡ በዘርፉ በሕዝብ ስም የሚመጣው ሀብትና ንብረት በግባቡ ለታለመለት ዓላማ መዋል ከቻለ የበጎ አድራጎት ድርጀቶችና ማኅበራት በጥቅሉ ሊያበረክቱት የሚችሉት አስተዋጽኦ ምን ያህል ሊሆን እንደሚችል በቀላሉ መረዳት አያዳግትም፡፡

ነገር ግን ሁሉም የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ሕግ በሚፈቅደው መልኩ ከአገር ውስጥና ከአገር ውጭ የሚሰበስቡትን ገንዘብ በትክክል ለሚፈለገው ዓላማ እያዋሉት ነው ወይ የሚለው ጥብቅ ክትትል የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡ ለአገር ዕድገትና ብልፅግና የሚሠሩ እንዳሉ ሁሉ ልማትን ሽፋን በማድረግ በአቋራጭ ለመክበር የሚንቀሳቀሱ አካላት መኖራቸው ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ በአገሪቷ ያሉ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ተልዕኳቸው ስኬትማ የሚሆነው ግልጽነትና ተጠያቂነት በሰፈነበት አሠራር መሠረት ተንቀሳቅሰው በቀጥታ ኅብረተሰቡ ከልማት ሥራቸው ተጠቃሚ መሆን ሲችል ነው፡፡ ይህ ዕውን የሚሆነው ሕግ በአግባቡ ተግባራዊ ሲደረግ ነው፡፡ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ለአገር ካላቸው ጠቀሜታ አንፃር ተገቢው ድግፍ ሊደረግላቸው ይገባል፡፡ ሕግን ተረድተው በአግባቡ እንዲሠሩ ድጋፍ ከተደረገላቸው አቅም ፈጥረው አገሪቷ ሁለተኛውን የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዕውን ለማድረግ በምታደርገው ርብርብ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት ይችላሉ፡፡

ከአዘጋጁ፡-ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

Standard (Image)

ሙስና ሰላምና መረጋጋት እንዲጠፋና ግጭቶች እንዲስፋፉ በር ይከፍታል

$
0
0

በዳዊት ወልደሱስ

ስለሙስና ብዙ ጊዜ እንሰማለን፡፡ አቶ እገሌ ወይም ወ/ሮ (ወ/ሪት) እገሊት በሙስና ተጠርጥረው ፍርድ ቤት ቀረቡ፣ በሙስና ወንጀል ታሰሩ፣ ይህን ያህል ካሳ እንዲከፍሉ ተፈረደባቸው፣ ወዘተ ሲባል በሚዲያ በተደጋጋሚ አዳምጠናል፡፡ ሙስና ማለት ምን ማለት ነው?

ሙስና የግእዝ ቃል ሲሆን ‹‹ማሰነ››፣ ጠፋ ወይም ጥፋት የሚል ትርጉም አለው፡፡ ይህ የማይገባ ድርጊት መፈጸም መሆኑን ያመላክታል፡፡ የተለያዩ የመረጃ ምንጮችም ለቃሉ ይስማማዋል የሚለውን ትርጉም ሰጥተውታል፡፡ ለአብነትም ኦክስፎርድ የእንግሊዝኛው መዝገበ ቃላት አደራን አለመጠበቅ፣ እምነትን ማጉደል፣ በጉቦ፣ በምልጃና በአድልዎ ሀቅን፣ ውሳኔንና ፍትሕን ማዛባት በማለት ለሙስና ትርጉም ሰጥቶታል፡፡ ለግል ወይም ለቡድን ጥቅም ሲባል ሥርዓቶችን፣ ሕጎችን፣ ደንቦችን፣ አሠራሮችን፣ መርሆዎችን የመጣስ ማንኛውም ተግባር ሙስና ይባላል፡፡ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ልማት ትብብር ድርጅትም በበኩሉ ሙስና በመንግሥትና በሕዝብ የተሰጠን ሥልጣንና ኃላፊነት ለግል ጥቅም ወይም ሌላን ለመጥቀም ወይም ለመጉዳት ሲባል ያላግባብ መገልገል ነው ይላል፡፡

እያንዳንዳችንም ትርጉም እንስጠው ብንል ከግብሩ የተነሳ በይዘት ረገድ ተቀራራቢ ፍቺ ልንሰጥ እንደምንችል እገምታለሁ፡፡ በአጭሩ ሙስና ሕግና ሥርዓትን ተከትሎ ከመሥራት ይልቅ ሥልጣንና ኃላፊነትን በመጠቀም ሕግና ሥርዓትን በመጣስ የመንግሥትና የሕዝብ ሀብትና ንብረትን መስረቅ፣ መዝረፍ፣ ማጭበርበር እንዲሁም በጉቦ፣ በዝምድና፣ በትውውቅ፣ በጎሰኝነት፣ በፖለቲካ ወገንተኝነትና በሃይማኖት ትስስር ላይ በመመርኮዝ አድሏዊ በሆነ አሠራር ፍትሕን እያዛቡ የግል ጥቅምን ማካበትና ሌላውን ወገን ተገቢ ባልሆነ መንገድ መጥቀም፣ መጉዳት የሚለው ገለጻ ሊያግባባ ይችላል፡፡

ከትርጉሙ እንመለስና የሙስና ውልደቱ ከየት ነው? በአካል ገዝፎ፣ በሰውና በአገር ላይ ጠባሳውን የሚያሳርፈውስ እንዴት ነው? ሊቃውንቱ ኪራይ ሰቢሳቢነት በአመለካከት ተወልዶ ወደ ተግባር ካደገ በኋላ ሙስና ይሆናል ይላሉ፡፡ ይህ ማለት ሙስና በግብር እንዲገለጥ የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከት ወሳኝነት አለው ማለት ነው፡፡ ስለኪራይ ሰብሳቢነት ለማስገንዘብ የተጻፉ ሰነዶች እንደሚነግሩንም ኪራይ ሰብሳቢነት ግላዊ ወይም የቡድን ፍላጎትን በሕገወጥ መንገድ ለማሟላት መልካም ሥነ ምግባር በሌላቸው ሰዎች የሚፈጸም ተግባር ሲሆን፣ ዋነኛው መንስዔውም ከፍተኛ የሆነ የሥነ ምግባር ዝቅጠት መሆኑን ይጠቁማሉ፡፡

ለአብነትም የመስረቅና የስግብግብነት ባህሪ መኖር፣ ሳይሠሩ መክበር፣ የተደላደለና የተንደላቀቀ ሕይወት የመኖር ፍላጎት፣ ለተለያዩ ሱሶች መጋለጥ፣ ግለሰቦች ከሌሎች ጋር ራሳቸውን ሲያወዳድሩ የሚሰማቸው የበታችነት ስሜት፣ ከሕግ በላይ የመሆን ስሜት መኖርና ሕጋዊ ዕርምጃ ሊወሰድባቸው እንደማይችል መገመት፣ ኃላፊነት የማይሰማቸው እየሆነ መሄድ ወይም የግድ የለሽነት ባህሪ እያዳበሩ መሄድ በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ስለሆነም ሙስና የተፈጥሮ ሰብዕናን ለሌላ ባዕድ ነገር ራስን በማስገዛት ኢ-ሥነ ምግባር ለሆነው ድርጊት ባሪያ መሆን ነው፡፡ ይህ ደግሞ በግለሰብ ደረጃ ሀብታም ወይም ደሃ መሆን፣ ባለሥልጣን ወይም ተራ ሠራተኛ መሆን፣ ፖለቲከኛ ወይም ሃይማኖተኛ መሆን፣ ትልቅ ወይም ትንሽ መሆንን አይመለከትም፡፡ ማንም ሰው የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከት ካለው ያ አመለካከት ወደ ተግባር ያመራዋል፡፡ ያ ደግሞ ሙስና ይሆናል፡፡ በአገር ደረጃም የበለፀጉ፣ ያልበለፀጉ በሚል የሒሳብ ቀመር የሚሠራለት አይደለም፡፡ በአመለካከት ተወልዶ በተግባር የሚገለጥ ነውና!

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀረ ሙስና ኮንቬንሽንም (The United Convention Against Corruption) ሙስና በሁሉም አገሮች (በሃብታሙም በደሃውም፤ በትልቁም በትንሹም…) የሚገኝ ክፉ ክስተት (Evil henomena) ነው ይለዋል፡፡ ክስተቱም ዘርፍን ሳይለይ የሚገለጥ ነው፡፡ በፖለቲካ ዓለም ወይም በሃይማኖትም ሊሆን ይችላል፡፡ ብቻ የሥነ ምግባር ዝቅጠት በተከሰተበት ሙስና ይኖራል፡፡

ለዚህ ነው አገራችንም ምንም እንኳ በዕድገት ጎዳና ያለች ብትሆንም ይህን ክፉ ጠላት ለመዋጋት በሜክሲኮ ከተማ የዓለም አገሮች የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀረ ሙስና ኮንቬንሽንን እ.ኤ.አ. በዲሴምበር 9 ቀን 2003 ሲፈራረሙ ከአፅዳቂ አገሮች አንዷ የሆነችው፡፡ ሙስናን አምርራ ለመታገል!

በአገራችን በየዘመናቱ በሚነሱ መንግሥታት ሙስና እንደ አረም በአገሪቱ እየበቀለ በዕድገት ላይ ማነቆ በመሆን የምንፈልጋትን የበለፀገች ኢትዮጵያን ለማምጣት፣ እንዲሁም ወደ ቀደመ ክብሯ እንዳትመለስ እንቅፋት በመሆን ዘመናትን ተሻግሯል፡፡ አሁንም ውስጥ ለውስጥ እንደ አሜባ እየተከፋፈለ ቀጥሏል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ እኔ ብቻ በአቋራጭ ልበልፀግ የሚለውን ክፉ አስተሳሰብ ተሸክመው በሚጓዙ ግለሰቦች ያለማቋረጥ ክፋቱ እየጨመረ በመሄዱ ነው፡፡

በየጊዜው አስፈላጊው ዕርምጃ በጥፋተኞች ላይ ቢወሰድም ችግሩን ለማጥራት ግን አስቸጋሪ ሆኗል፡፡ በየጊዜው በአገር ሀብት ላይ የሚካሄደው ዘረፋንም ለመቆጣጠር ፈታኝ ሆኗል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የስርቆት ባህሪው እንደ እስስት መልኩን እየቀያየረ መሄዱ ነው፡፡ ለዚህ ነው የሰውን አመለካከት በቀላሉ ለማወቅ አስቸጋሪ በመሆኑ ሙስና በተግባር እየተወለደ የሕዝብና የአገር ሀብት እየተዘረፈ የሚገኘው፡፡

በማደግ ላይ በምትገኝ አገር ደግሞ ይህ ክፉ ጠላት ብርሃኗን ሊያጨልም እንደሚችል ጥርጥር የለውም፡፡ በዓለም አገሮች ምስክርነትን ያገኘው የአገራችን የኢኮኖሚ ዕድገት ፈጣን በመሆኑ በ2017 ዓ.ም. መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ ለመሠለፍ እንደሚያስችለን አመላካች ነው፡፡ ይህን ዕድገት የሚያስቀጥሉ በርካታ የልማት ሥራዎች እየተሠሩ እንደሚገኙም የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ይህ ዕድገት በሕዝቦች መካከል ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል ለማምጣትና ድህነትን እስከወዲያኛው ለመፋታት መንገዱ ተጀምሯል፡፡ ነገር ግን ኪራይ ሰብሳቢነትና ሙስና ብርሃኗን ሊያጨልሙ፣ ዕድገቷን ሊገቱና ሰላሟን ሊነሱ ፊት ለፊት ተጋርጠዋል፡፡

ለዚህ ነው የኪራይ ሰብሳቢነት ፖለቲካል ኢኮኖሚ አመለካከትና ተግባር በአገራችን እየተመዘገበ ላለው የኢኮኖሚ ዕድገት እንቅፋት ናቸው ተብለው ከተለዩት ዋነኛ ችግሮች ውስጥ አንደኛው የሆነው ነው፡፡ ችግሩ በኢኮኖሚ ዕድገቱ ላይ ብቻ ያነጣጠረ ሳይሆን፣ እየተገነባ ላለው የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታም ጠንቅ መሆኑን በተለያዩ መድረኮች ተገምግሞ ተረጋግጧል፡፡ ይህን የኪራይ ሰብሳቢነት የበላይነት ለመናድና በልማታዊ የፖለቲካ ኢኮኖሚና አስተሳሰበ ለመተካት ደግሞ የሁሉንም ሰው ርብርብ የሚጠይቅ ነው፡፡ ካልሆነ ሕዝብ በመንግሥትና በሕግ የበላይነት ላይ አመኔታ እንዲያጣ፣ በዴሞክራሲ ሥርዓት ላይ ጥርጣሬ እንዲኖረውና ፖለቲካዊ አለመረጋጋት እንዲሰፍን ያደርጋል፡፡ ልማት እንዲቀጭጭ፣ የአገር ኢኮኖሚ ዕድገት እንዲገታና ድህነት እንዲስፋፋም መንገድ ይከፍታል፡፡

አሁን ይህ የተዛባና ጤናማ ያልሆነ አመለካከት ሊስተካከል ይገባል፡፡ ስለኪራይ ሰብሳቢነትና ሙስና ብዙ ከማውራት በተግባር ማስተካከል ይገባል፡፡ ማንም አካል በሚያከናውነው እኩይ ተግባርም አስፈላጊውን ሕጋዊ ቅጣት ማግኘት ይኖርበታል፡፡ ችግሩን ለመከላከልም ጉዳዩን ለመንግሥት ብቻ መስጠት ተገቢ አይሆንም፡፡ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል በጉዳዩ ላይ የራሱን ሚና ሊጫወት ይገባል፡፡ አገር የሕዝብና የመንግሥት ናትና፡፡

ከድህነት መውጣት የማይፈልግ አይኖርም፡፡ ከድህነት በመውጣት የበለፀገች አገር መገንባት የሚቻለው ደግሞ ጠላትን በተባበረ ክንድ መቋቋም ሲቻል ነው፡፡ ‹‹ድር ቢያብር …›› አይደል ተረቱ፡፡ ድህነትን አምርሮ የሚጠላ ሕዝብ እንዲኖር ደግሞ አመለካከት ላይ በስፋት መሠራት እንዳለበት ሁሉንም የሚያግባባ ሐሳብ ነው፡፡ አመለካከት ከተቀየረ ቀሪው ነገር ሁሉ በሚፈለገው ደረጃና ፍጥነት ይሄዳል፡፡ ሙስናም ከመወለዱ በፊት ይመክናል፡፡ ስለሆነም በዕድገት ላይ ያለው ሥጋት ይቀንሳል፡፡

የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከት ካልተቀረፈ ሙስና በየጊዜው በዝቶ መወለዱ አይቀርም፡፡ ድርጊቶች የሚገለጡት ‹‹ላድረገው?›› በሚል የሐሳብ መነሻነት ነውና፡፡ ስለሆነም አገራችን እያደረገችው ላለው የህዳሴ ጉዞ መሰናክልነቱ የበረታ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ ሰላምና መረጋጋት እንዲጠፋ፣ የጥቅም ግጭቶች እንዲስፋፉ፣ አገራዊ ስሜት እንዳይኖር፣ አንዱ በሌላው ላይ ግፍ እንዲፈጽም፣ ሰብዓዊነት እንዳይኖርና አንዱ በሌላው ላይ እንዲነሳ ያደርጋል፡፡

‹‹ችግርን ለይቶ ማወቅ የጉዳዩን ግማሽ በመቶ መፈጸም›› እንደሆነ ይነገራል፡፡ ትክክል ነው፡፡ ኪራይ ሰብሳቢነትና ሙስና የአገራችን ሥርዓት አደጋ መሆኑ ተለይቷል፡፡ ቀሪው በችግሩ ላይ በኅብረት መዝመት ነው፡፡ ያኔ ሥጋቱ ይቀንሳል፡፡ የምናልማትን የበለፀገች ኢትዮጵያን ለትውልድ እናወርሳለን፡፡

ከአዘጋጁ፡-ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው dawit.keha@gmail.comማግኘት ይቻላል፡፡

 

Standard (Image)

‹‹አወቅሽ…አወቅሽ ሲሏት መጽሐፉን አጠበች››

$
0
0

(ክፍል አንድ)      

 
በመሓሪ ይፍጠር

የቀድሞው የአየር ኃይል አዛዥ የነበሩትና የዛሬ 15 ዓመት ገደማ ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ሕወሓት ውስጥ በአንድ በኩል በልማታዊ ዴሞክራሲ ኃይሎች፣ በሌላ በኩል ደግሞ በትምክህት፣ በጥበትና በኪራይ ሰብሳቢነት ጎራ መካከል በተካሄደው የሐሳብ ፍትጊያ ኪራይ ሰብሳቢነትን ከሚያቀነቅነው ‹‹አንጃ›› ጋር ተሠልፈውና እንደ ሠራዊት አባል ለሕገ መንግሥቱ ታማኝ ባለመሆናቸው ምክንያት ከሥራቸው የተሰናበቱትን ግለሰብ አንድ ጽሑፍ እንደ ዋዛ አነበብኩ፡፡ በቅፅል ስማቸው ‹‹ጆቤ›› እየተባሉ የሚጠሩት ጡረተኛው ሜጀር ጄኔራል አበበ ተክለሃይማኖትን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የተጻፈ ደብዳቤ ነው። 

በሕወሓት ክፍፍል ወቅት ሕገ መንግሥቱን ተፃርረው በፖለቲካ ጉዳዮች ውስጥ ጭልጥ ብለው ገብተው የነበሩት የእኚሁ ግለሰብ ደብዳቤ ይዘት፣ ‹‹ሕገ መንግሥቱን የሚፃረረው የሠራዊት ግንባታ ሰነድ ከሥራ ይወገድ›› የሚል ነው። ምንም እንኳን የ‹‹ጆቤ›› ደብዳቤ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተጻፈ ቢሆንም፣ በደብዳቤያቸው ላይ ‹‹ከሥራ ይወገድ›› በማለት የጠቀሱት ሰነድ ላይ የሰነዘሯቸው ሐሳቦች አሁንም ሰውዬው ከቀደምት አስተሳሰባቸው ያልተላቀቁና የጠቀሱትን መፅሐፍ አዋቂ በመምሰል በውሸት አስተሳሰብ ለማጠብ በመሞከራቸው፣ እንደ ዜጋ ይህን ምላሽ ለመስጠት ብዕሬን ከወረቀት ጋር አዋድጃለሁ።

እርሳቸው እንዳሉትና እኔም መጽሐፉን ፈልጌ እንዳነበብኩት ‹‹የሠራዊት ግንባታ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ›› የተሰኘው ሰነድ ባለ 209 ገጽና በብራና ማተሚያ ድርጅት የታተመ ነው። እርሳቸው ከጠቀሷቸው እውነቶች ውስጥ አንዱ ይኸው ጉዳይና ግለሰቡ ባያምኑበትም ‹‹ሠራዊቱ በሕገ መንግሥቱና በሕገ መንግሥቱ ብቻ መመራት አለበት›› የሚለው አፋዊ ትረካቸው ይመስለኛል። የተቀሩት እሳቤዎች ግን በሐሳብ መንትዮቻቸው ‹‹አወቅክ…አወቅክ…›› ሲባሉ መጽሐፉን በኒዮሊበራል አስተሳሰብ የማጠብ ጥረት ብቻ ሆኖ ነው ያገኘሁት። ከዚህ እልፍ ሲልም የመከላከያ ሠራዊቱን ከፍተኛ መኮንኖች በውሸት ኢ-ሕገ መንግሥታዊ አድርጎ የመሳል አባዜንም ያካተተ ነው። እንዲያውም በተሃድሶው መስመር ተጉዘው ውጤታማ በመሆን ላይ ያሉትን ሥርዓቱንና ሠራዊቱን በሚያስገርም ሁኔታ በደርግነት እስከ መፈረጅ ይደርሳል። ይህም ግለሰቡ ዛሬም ቢሆን የተሃድሶው መስመር እንቅፋት ለመሆን መከጀላቸውን የሚያመላክት ይመስለኛል።

ጡረተኛው ሜጀር ጄኔራል ‹‹የአገራችን መከላከያ ተቋም ሕገ መንግሥቱና ሕገ መንግሥቱን ብቻ መሠረት አድርጐ መንቀሳቀስ ሲገባው፣ በግላጭ ሕገ መንግሥቱን የመጣስ ክስተቶች እየታዩ ነው›› በማለት ተቋሙን ይከሳሉ። ለክሳቸው ያቀረቡት ማስረጃ ግን የለም። ምናልባት እርሳቸው በደፈናው ‘ውንጀላዬ ካለፈው ደርግ መጣ፣ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ጠንቀቅ በሉ ከሚለው ጽሑፌ የቀጠለ ነው’ የሚሉን ከሆነ፣ ይህን ጽሑፋቸውን ‹‹ክፍል ሁለት›› ብለው ሊያቀርቡልን በተገባ ነበር። ይህን ግን አላደረጉትም። ያም ሆኖ ግን እርሳቸው ‹‹ደርግ መጣ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ጠንቀቅ በሉ›› ለሚለው ጽሑፋቸው መነሻ የሆናቸው የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም ጄኔራል ሳሞራ የኑስ በመቐለ ከወጣቶች ጋር ያደረጉት ተሞክሮ የማስተላለፍ ውይይትን ተከትሎ ነው።

ታዲያ በወቅቱ እኔም የ‹‹ጆቤ››ን ሐሳብ ተንተርሼ በኢንተርኔት ላይ የተጫነ ነገር እንዳለ ፈትሼ ነበር። በትግርኛ የተካሄደውን ውይይትም አገኘሁት። ትግርኛ ሁለተኛ ቋንቋዬ በመሆኑም የውይይቱን መንፈስ በሚገባ ተረድቼዋለሁ። የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም ጄኔራል ሳሞራ የኑስን በአካል አላውቃቸውም። አልፎ አልፎ በቴሌቪዥን መስኮት ካልሆነ በስተቀር እርሳቸውን የማግኘት ዕድሉም አላጋጠመኝም። ጡረተኛውን ሜጀር ጄኔራል አበበ ተክለሃይማኖትንም በጽሑፋቸው እንጂ በአካል አግኝቻቸው አላውቅም። ሁለቱንም ባገኛቸውና ሐሳባቸው ምን እንደሆነ ብረዳ ጥሩ ነበር። ሆኖም የሚያገናኘን ነገር ባለመኖሩ ‹‹ጆቤ››ንም በጽሑፋቸው፣ ጄኔራል ሳሞራንም በወቅቱ ካስተላለፉት የተሞክሮ ውይይት አንፃር መልዕክቶቻቸውን ለመመልከት ሞክሬያለሁ።

ሆኖም ተሞክሮን ከሚያስተላልፈው ከጄኔራል ሳሞራ ውይይት ጡረተኛው ሜጀር ጄኔራል ‹‹ደርግ መጣ›› ሊያስብላቸው ያስቻላቸውን ነገር ማግኘት አልቻልኩም። እናም ‹‹ጆቤን›› ልታዘባቸው የግድ ብሎኛል። ምክንያቱም እርሳቸው እንዳሉት በኤታ ማዦር ሹሙ ንግግር ምክንያት የተጣሰ ሕገ መንግሥትም አላገኘሁም፡፡ በሕገ መንግሥቱ ላይ ‘ወጣቶች አገራዊ ፍቅር እንዲያድርባቸው አንድ ጄኔራል መኮንን ተሞክሮውን ማካፈል አይችልም፣ ስለሚመራው መሥሪያ ቤትም የመናገር መብት የለውም’ የሚል ድንጋጌ ተፅፎ ባለማየቴ ነው። እንዲሁም ‹‹ጆቤ›› ውይይቱን ተከትለው ‘የጄኔራሉ ንግግር ሕገ መንግሥቱን የሚፃረር ነው’ ለማለት የፈለጉበት መንገድ ከራሳቸው የጥላቻ ምናብ ተነስተው መሆኑን ለመገንዘብ ጊዜ አልወሰደብኝም። እናም በዚያ አስተያየታቸው እኔ በእርሳቸው ቦታ ሆኜ ማፈሬን ልደብቃቸው አልሻም። 

ለነገሩ ስለውትድርና ምንም ዓይነት ዕውቀት ባይኖረኝም እንዲሁ ሳስበው ግን አንድ ጄኔራል መኮንን እንደ ዜጋ የሚያቀርባቸው ሐሳቦች እንደምን ሕገ መንግሥቱን ጥሷል ሊያስብል እንደሚችል ግልጽ ሊሆንልኝ አልቻለም። እንዲሁ ዝም ብዬ ስገምት ግን ጄኔራል ሳሞራ ከተራ ታጋይነት እስከ የአንድ አገር ሠራዊት ኤታ ማዦር ሹምነት ድረስ የደረሱ፣ ለዚያውም በአገራችን ታሪክ ለሕዝቦች ባበረከቱት አስተዋፅኦ የሙሉ ጄኔራልነት ማዕረግ ማግኘት የቻሉ ብቸኛው ኢትዮጵያዊ ይመስሉኛል። ታዲያ በዚህ የሕይወት ጉዟቸው ውስጥ በርካታ ድሎችንና ውጣ ውረዶችን ያሳለፉ፣ ራሳቸውን በየጊዜው በልምድና በትምህርት ያበቁና ዛሬ ላሉበት የኃላፊነት ደረጃ የደረሱ በመሆናቸው የካበተ ተሞክሮ ያላቸው ሊሆኑ እንደሚችሉ ለመገመት የሚከብድ አይመስለኝም። እርግጥም ጄኔራል መኮንኑ በኤታ ማዦር ሹምነት እየመሩ ያሉትና በዓለም አቀፍ ደረጃ ‹‹አንቱታን›› የተቸረው እንዲሁም በተሰማራባቸው በአገር ውስጥም ይሁን በውጭ ግዳጆች በሕዝባዊነቱ ከበሬታን ያተረፈ ሠራዊትን፣ በሕገ መንግሥቱና በሕዝባዊ ወገንተኝነት እምነቱ ፅናትንና ጀግንነትን እንዲላበስ በማድረግ ብሎም ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ሠራዊቱን በማዘመን ረገድ እርሳቸውና የሥራ ባልደረቦቻቸው የላቀ ሚና የተጫወቱ ይመስለኛል።

እናም በእኔ እምነት ወጣቶች ከእኚህ እጅግ የካበተ ልምድና ተሞክሮ ካላቸው ጄኔራል መኮንን ተሞክሮ ያገኙ ዘንድ መጋበዛቸውና እርሳቸውም በውይይቱ ላይ መገኘታቸው ኃጢያቱ ምን እንደሆነ ለማንም የሚገባ አይመስልም። በእኔ እምነት በዚህ ዓይነት ውይይት ላይ እንኳንስ ኤታ ማዦር ሹሙ ቀርቶ፣ ጡረተኛው ሜጀር ጄኔራል አበበም ቢሆኑ ከክፍፍሉ በፊት የነበራቸውን ጤነኛ አመለካከት ለወጣቶች ቢያስረዱ ክፋት ያለው አይመስለኝም። እርግጥ የ‹‹ጆቤ›› ፍላጎት ቀደም ሲል የጠቀስኩትንና አመቺ ነው ተብሎ በታሰበ ወቅት የተሃድሶውን መስመር ማደናቀፍ በመሆኑ፣ በተለያዩ ጉዳዩች ላይ ውሸትን እየቀመሩ መጻፋቸው ብዙም የሚደንቅ አይመስለኝም።

ጡረተኛው ሜጀር ጄኔራል ‹‹የሠራዊት ግንባታ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ›› የሚለውን መፅሐፍ ሲያነቡ እርሳቸው በምናባቸው ውስጥ የፈጠሩት የሠራዊቱ ኢ-ሕገ መንግሥታዊነት በከፊልም ቢሆን መሠረታዊ ችግሩ የት ላይ እንደሆነ እንደተገለጠላቸው ሊነግሩን ሞክረዋል። በእርሳቸው እምነት የችግሩ ምንጭ በሰነዱ ላይ ሠራዊቱ የገዥው ፓርቲ ‹‹የመጨረሻው ምሽግ›› እንዲሆን ወይም ‹‹ቀባሪው እንዳይሆን›› ሆኖ መገንባቱ ነው። ይሁንና እንዲህ ዓይነቱ የሠራዊት አገነባብ መንገድ ለእርሳቸው እንዴት አዲስ እንደሆነባቸው ግልጽ አይደለም፡፡ በየትኛውም አገር ውስጥ ቢሆን የሚሠራበት አካሄድ ነውና።

አንድ አገር የሚከተለው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ሥርዓት ፊውዳላዊም ይሁን አብዮታዊ ዴሞክራሲ አሊያም ሊበራል ዴሞክራሲ ወይም ሃይማኖታዊ ወይም ሌላ፣ ሠራዊቱን የሚቀርፀው የሥርዓቱ ነፀብራቅ እንዲሆን አድርጎ ነው። ሊበራል ዴሞክራሲን በሚከተሉ አገሮች ውስጥ ሠራዊቱ የሚገነባው በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ርዕዮተ ዓለም እንደማይሆነው ሁሉ፣ አብዮታዊ ዴሞክራሲን በሚከተል ሥርዓት ውስጥም ሊበራል ዴሞክራሲን የሚያቀነቅን ሠራዊት ሊገነባ አይችልም። ሃይማኖታዊ በሆኑ ሥርዓቶች ውስጥም ‹‹መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው›› የሚል ሴኩላሪዝምን የሚያቀነቅን ሠራዊት ሊገነባ አይችልም። ከዚህ አኳያ አገራችን ውስጥም ሠራዊቱን በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ርዕዮተ ዓለም መገንባት የቆመለትን ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት በፅናት እንዲጠብቅ የሚያደርገው እንጂ፣ ከሕገ መንግሥቱ ጋር የሚያጋጨው አይደለም። እናም ጡረተኛው ሜጀር ጄኔራል አበበ በሑፋቸው ላይ ከሰነዱ ጠቅሰው፣ ‹‹እኛ የምንገነባው የመከላከያ ኃይል የአብዮታዊ ዴሞክሪሲያዊ ሥርዓታችን ዘብ ነው ብለን በግልጽና በጥሬው ማስቀመጥ አስፈላጊ ነው›› የሚለውን አባባል፣ ‹‹ምን ዓይነት እብሪት ነው?›› በማለት የገለጹበትን ጨዋነት የጎደለውን አባባላቸውን ያስተካክሉታል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። ሌሎች ከመጽሐፉ የጠቀሷቸውንና ‹‹ለምን ሠራዊቱ በአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ርዕዮተ ዓለም ይመራል?›› ብለው ለመሞገት ሲሉ ያነሷቸውን ጉዳዩችንም ከዚሁ አኳያ እንደሚያዩዋቸው በመተማመን።

ያም ሆነ ይህ ግን ዕውነታውን ለመረዳት በቅድሚያ ‘ሕገ መንግሥቱ ስለ ሠራዊቱ ምን ይላል?’ ብሎ መጠየቅ የሚገባ ይመስለኛል። በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 87 ላይ ‹‹የመከላከያ መርሆዎች›› በሚል ርዕስ ሥር አምስት ድንጋጌዎች ተቀምጠዋል። እነርሱም የአገሪቱ መከላከያ ሠራዊት የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ሚዛናዊ ተዋፅኦ ያካተተ ይሆናል፣ የመከላከያ ሚኒስትር ሆኖ የሚሾመው ሲቪል ይሆናል፣ የመከላከያ ሠራዊት የአገሪቱን ሉዓላዊነት ከመጠበቅ በተጨማሪ በዚህ ሕገ መንግሥት መሠረት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚሰጡትን ተግባሮች ያከናውናልና የመከላከያ ሠራዊቱ ተግባሩን ከፖለቲካ ድርጅቶች ወገናዊነት ነፃ በሆነ አኳኋን ያከናውናል የሚሉ ናቸው። ሕገ መንግሥት ጥቅል ሐሳቦችን የያዘ እንደመሆኑ መጠን በዝርዝር አዋጆችና ደንቦች መደገፉ የግድ ነው። እናም መንግሥት የሠራዊቱን ሕገ መንግሥታዊ ሚና ይበልጥ ለማጠናከር በአዋጅ ቁጥር 27/1988 የመከላከያ ሠራዊቱን አቋቁሟል።

ታዲያ እዚህ ላይ ሳልጠቀስ የማላልፈው ነገር ቢኖር የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት በአገር ውስጥ ፀጥታ የማስጠበቅ ተግባር የሚሰማራው የችግሩ ሁኔታ ከፖሊስ አቅም በላይ ከሆነ አሊያም ሊሆን ይችላል ተብሎ በመንግሥት በኩል ሲታመንበት ነው። በተለይም ከክልሎች አቅም በላይ የሆነ የፀጥታ መደፍረስ ችግር ሲያጋጥምና ክልሉ የፌዴራል መንግሥቱን ድጋፍ ሲጠይቅ ሠራዊቱ ጣልቃ ሊገባ ይችላል። ከዚህ በተጨማሪ ጡረተኛው ሜጀር ጄኔራል ከፖለቲካ ገለልተኛ መሆን ሲገባቸው ይህን ባለመፈጸማቸው ሳቢያ ከሠራዊቱ በጡረታ በመገለላቸው አላውቀውም ካላሉ በስተቀር፣ የሠራዊቱን ሕገ መንግሥታዊ ሚና አስመልክቶ በአዋጅ ቁጥር 395/1995 ድንጋጌ ወጥቷል።

ይህ ድንጋጌ ሠራዊቱ ምን ያህል ሕገ መንግሥቱን ብቻ ተመሥርቶ ተግባሩን እንደሚያከናውን የሚያሳይ ነው። ይኸውም አዋጁ ሠራዊቱ ለሕገ መንግሥቱና ለሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱ መከበር ዘብ እንደሚቆም፣ የአገር ሉዓላዊነትን እንደሚያስከብር፣ በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጡትን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን የማክበር፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን አደጋ ላይ የሚጥሉ ማናቸውንም እንቅስቃሴዎች መከታተልና በመንግሥት ሲታዘዝ አደጋውን ለማምከን መሥራት፣ እንዲሁም የተጣለበትን ኃላፊነት በሕግና በሕግ ብቻ የመወጣት ግዴታ ጥሎበታል።

ጡረተኛው ሜጀር ጄኔራል ሠራዊቱን ኢ-ሕገ መንግሥታዊ አድርገው ለመሳል ቢሞክሩም መሬት ላይ ያለው ዕውነታ ግን ይህ አይደለም። ሠራዊቱ ለሕገ መንግሥቱና ለሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱ ያለው ታማኝነት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ሰላማዊ ሠልፍ እንደማያደርግና ሌሎች በሚጠሩት ሠልፎችም ላይ እንደማይገኝ፣ የፖለቲካ ፓርቲ አባል መሆን እንደማይችል፣ በስውርም ይሁን በግልጽ የፖለቲካ ቅስቀሳ ማድረግ እንደማይችል፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችን በመቃወምም ይሁን በመደገፍ ቅስቀሳ እንደማያደርግ፣ የመምረጥ መብት ቢኖረውም በግሉም ይሁን የፖለቲካ ፓርቲን ወክሎ ሥልጣን እንደማይዝ፣ እንዲሁም ለፖለቲካ ፓርቲዎች የገንዘብ ድጋፍ እንዳማያደርግ በሠራዊቱ መተዳደሪያ ደንብ ላይ ገደብ ተጥሎበታል። እንግዲህ እነዚህ ኃላፊነቶች፣ ግዴታዎችና ገደቦች በሕገ መንግሥቱና ሕገ መንግሥቱን ተመርኩዘው የሠራዊቱን ተልዕኮዎች በተዘረዘረ መልኩ ለመግለጽ የወጡት አዋጆች፣ ሠራዊቱ ሕገ መንግሥታዊ አደራና ግዴታ ያሉበት እንጂ ጡረተኛው ጄኔራል መኮንን በደፈናው ሠራዊቱን ለመክሰስ ሲሉ ለማለት እንደከጀሉት ሠራዊቱ የሚመራባቸው ሰነዶች ኢ-ሕገ መንግሥታዊ መሆናቸውን የሚያሳዩ አይደሉም።

እናም እነዚህን ሕገ መንግሥታዊና ከሕገ መንግሥቱ መንጭተው የወጡ አዋጆችንና ደንቦችን በሠራዊቱ ውስጥ የማስረፅ (Indoctrinate) ሥራን ለማከናወን በመንግሥት ደረጃ አንድ ሰነድ ተዘጋጅቶ መመርያ መሆን እንዳለበት ግልጽ ነው። ለዚህም ይመስለኛል ‹‹የሠራዊት ግንባታ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ›› የሚለው ሰነድ የሠራዊቱ የግንባታ መመርያ ሆኖ የተዘጋጀው። ታዲያ የሰነዱን አስፈላጊነት በዚህ ደረጃ ከተማመን ዘንዳ፣ አሁን ደግሞ ጡረተኛው ሜጀር ጄኔራል አበበ ይህን ሰነድ ‹‹ኢ-ሕገ መንግሥታዊ ነው›› በማለት ወዳነሷቸው ጉዳዩች ላምራ። 

ማንኛውም የጡረተኛውን ጄኔራል መኮንን ጽሑፍ ያነበበ ሰው፣ ‹‹የሠራዊት ግንባታ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ የተሰኘው ሰነድ ሕገ መንግሥቱንና አብዮታዊ ዴሞክራሲ የሚለውን ርዕዮተ ዓለም በማደባለቅና በማምታት ስለሠራዊት ግንባታ ይዘባርቃል፤›› ከሚለው ኢ-ተዓማኒና አስገራሚ ሐሳብ ጋር መፋጠጡ አይቀርም። እኔም የተሰማኝ እንዲህ ዓይነት ስሜት ነው። ይሁንና በእኔ እምነት የተሃድሶውን መስመር ለማደናቀፍ ሁለት የማይነጣጠሉ ሰነዶችን (ሕገ መንግሥቱንና የሠራዊት ግንባታ ሰነዱን ማለቴ ነው) በግድ ለማለያየትና ሆድና ጀርባ አድርገው ለማቅረብ እያምታቱና እያዘባረቁ ያሉት ‹‹ጆቤ›› ይመስሉኛል። ምክንያቱም የሠራዊት ግንባታው ሰነድ በሕገ መንግሥቱ መሠረት ሕገ መንግሥቱን ለመጠበቅና ለመከላከል ሲባል የወጣ የአንድ ተቋም የግንባታ መመርያ እንጂ፣ ሕገ መንግሥቱን የሚፃረር ሆኖ ስላላገኘሁት ነው።

እርሳቸው ሠራዊቱ ለሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱ ያለውን ውግንና በተመለከተ በመጽሐፉ ገፅ 23 ላይ ‹‹ለአንድ ፓርቲ ዘብ በመሆን መልክ ሊገልጽ ይችላል። ከፓርቲው ውጪ ሆኖም ሥርዓቱን እንደ ሥርዓት ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ከመጠበቅ አንፃር ሊገለጽ ይችላል›› የሚለውን አባባል በመውሰድ፣ ሰነዱ ከሕገ መንግሥቱ የሚለይ ለማስመሰል ሞክረዋል። ይሁንና ሆን ብለው ከዚህ ዓረፍተ ነገር በላይ ያለውን ሊጠቅሱት አልፈለጉም። እርሳቸው ከጠቀሷቸው ዓረፍተ ነገሮች ከፍ ብሎ የተመለከተው ጉዳይ የሚያስረዳው፣ የአንድ አገር መከላከያ ኃይል አቅምና ጥንካሬ ሥርዓቱን እንዴት እንደሚከላከል የሚያትት ሲሆን፣ ሥርዓቱ አብዮታዊም ይሁን አድኃሪ እንዴት አድርጎ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን መጠበቅ እንደሚችልም የሚያመላክት ነው። ይህ የሠራዊቱ አቅምና ጥንካሬ የሕገ መንግሥቱን ደኅንነት መጠበቅና መከላከል በሚል ሊገለጽ እንደሚችልም ያብራራል። ታዲያ ጡረተኛው ጄኔራል ምን እያሉን ይሆን? እንዲህ ዓይነቱ ቅጥፈትስ ምን ይፈይዳል? ያም ሆነ ይህ እኔ በበኩሌ ሰውዬው የሦስተኛ ዲግሪ ተማሪ መሆናቸውን በተለያዩ ወቅቶች ደጋግመው ስለነገሩን፣ የሚማሩት ነገር ‹‹የሴራ ንድፈ ሐሳብ››ንም (Conspiracy Theory) ያካትታል እንዴ? ብዬ እንዳስብ አድርገውኛል።

‹‹ጆቤ›› በመጽሐፉ ገፅ 25 ላይ፣ ‹‹በእኛ ተጨባጭ ሁኔታ የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓታችንን ደኅንነት መከላከል ማለትና የአገር ደኅንነትን መከላከል ማለት በመሠረቱ አንድ ነው ማለት ይቻላል፤›› መባሉንም ሕገ መንግሥቱን የሚቃረን አስመስለው አቅርበዋል። በእኔ እምነት ይህ አስተሳሰባቸው ትክክል አይደለም። ለዚህም ሁለት ምክንያቶችን ማንሳት እችላለሁ። አንደኛው ቀደም ሲል እንደጠቀስኩት በየትኛውም አገር እንደሚደረገው የሠራዊት ግንባታንና አንድን ሥርዓት ለያይቶ ማየት አለመቻሉ ነው። ሁለተኛው ደግሞ ጡረተኛው ሜጀር ጄኔራል ከመጽሐፉ ላይ ቀንጭበው ከመውሰድ ውጪ እርሳቸው ስላነሱት ጽንሰ ሐሳብ በመጽሐፉ ላይ ምን እንደተባለ ሆን ብለው ስለዘለሉት ነው። ሁለቱንም ምክንያቶቼን ዘርዘር አድርገን እንያቸውና ሰውዬው ምን እያሉ እንደሆነ እንመልከት።

በቅድሚያ በማንኛውም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት አገርን የሚመራው በሕዝብ የተመረጠ ገዥ ፓርቲና እርሱ የሚከተለው ርዕዮተ ዓለም መሆኑን መገንዘብ የሚገባ ይመስለኛል። እናም በአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ አገሪቱን እየመራ ያለው የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ርዕዮተ ዓለም እንጂ፣ የኒዮ ሊበራል ሥርዓት ቀኖና አይደለም። ሥርዓቱ የሚመራበት ርዕዮተ ዓለምና የሠራዊት ግንባታ አንድ በመሆናቸውም፣ የአገር ደኅንነት የሚጠበቀው ይህንኑ ርዕዮተ ዓለም በሚያራምደው አካል መሆኑ ግልጽ ይመስለኛል። ይህም አገርን መጠበቅ ማለትና ሥርዓቱን መጠበቅ ማለት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን የሚያሳይ ነው። ይህ ማለት ግን ‹‹ጆቤ›› እንደሚሉት ሠራዊቱ በሥርዓቱ ርዕዮተ ዓለም ስለተገነባ ከሕገ መንግሥቱ ጋር ይጣረሳል ማለት አይደለም። ሌላ በሕገ መንግሥቱ መሠረት ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ ተወዳድሮና አሸንፎ የሚመጣ አካል ካለም፣ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ተፃርሮ እስካልቆመ ድረስ እርሱኑ መጠበቁ የሚቀር አይመስለኝም። እናም ጉዳዩን አጣሞ ለማቅረብ ካልተፈለገ በስተቀር ሀቁ ይኸው ነው። ውድ አንባቢያን ጡረተኛው ጄኔራል መኮንን ሰነዱን አስመልክተው ያነሷቸውን ሌሎች ጉዳዩችን በቀጣዩ ክፍል ጽሑፌ እመለስበታለሁ።

ከአዘጋጁ፡-ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው yimehari@yahoo.comማግኘት ይቻላል፡፡

 

Standard (Image)

ኢትዮጵያ በፖለቲካ መንታ መንገድ

$
0
0

በአይተን ጂ.

የኢሕአዴግ መንግሥት አገሪቱን ማስተዳደር ከጀመረበት ከ1983 ዓ.ም. ጀምሮ ታይቶ የማያውቅ በሚመስል ሁኔታ በተለያዩ አካባቢዎች ተከታታይ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች መታየት ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ከአዲስ አበባ የተቀናጀ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ  የተቀሰቀሱት የተቃውሞ ሠልፎች ምንም እንኳን ማስተር ፕላኑ በመንግሥት የተሰረዘ ቢሆንም አሁንም እንደቀጠሉ ናቸው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ ደግሞ የወልቃይትን የማንነት/የአስተዳደር ጥያቄ መነሻ በማድረግ ተከታታይ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች በአማራ ክልል እየተደረጉ ናቸው፡፡ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በተወሰዱ ዕርምጃዎችና ከተቃውሞ ሠልፎቹና እንቅስቃሴዎች ጋር በተያያዘ በተፈጠሩ ሁከትና ብጥብጦች የአገሪቱ ዜጎች ሕይወታቸውን አጥተዋል፣ ብዙዎች ለእስር ተዳርገዋል፣ ለድብደባና ለአካል መጉደል ተጋልጠዋል፣ ቤት ንብረታቸውም ወድሟል፡፡ የተቃውሞው እንቅስቃሴዎቹን ለማቀጣጠልም ሆነ ለማብረድ በሁሉም ወገኖች አሁን የሚወሰዱ ዕርምጃዎችና ቀጣይ ውሳኔዎች የአገሪቱን ዕጣ ፋንታና የዜጎቿን መፃኢ ዕድል በበጎም ሆነ በመጥፎ የመወሰን ዕድል የሚኖራቸው ይመስለኛል፡፡ ለዚህም ነው ይኼንን ጽሑፍ ኢትዮጵያ በፖለቲካ መንታ መንገድ የሚል አርዕስት የሰጠሁት፡፡

አዲስ ትውልድ - የከረመ ፍረጃ

የተቃውሞዎቹ መነሻ ምክንያቶችን በሚመለከት ብዙዎች ጽፈዋል፣ ተንትነዋል፡፡ የኢሕአዴግ መንግሥትም በአንድ በኩል ተቃውሞው ሕጋዊና ተገቢ እንደሆነና በዋነኝነት መልካም አስተዳደርን ባለማስፈኑና ሙስናን በአግባቡ ባለመዋጋቱ ምክንያት በሕዝብ ዘንድ ቅሬታ እንደተፈጠረ በተደጋጋሚ እየገለጸ ይገኛል፡፡ ሥርዓቱ ጠያቂ ትውልድ በመፍጠሩና በወጣቱ ዘንድ የፖለቲካ ንቃት በማደጉ ነው ይለኛል፡፡ በሌላ በኩል በውጭ የሚገኙ ፀረ ሰላም ኃይሎችና በሽብርተኛነት የተፈረጁ ጠባብና ትምክህተኛ ኃይሎች በሻዕቢያ መንግሥት አሰማሪነት የፈጠሩት ነው ሲል ይደመጣል፡፡ ይኼ ፍረጃ ኢሕአዴግ ሥልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ መሠረታዊ ልዩነት አለኝ የሚላቸው በአገሪቱ ያሉ ሌሎች የፖለቲካ ኃይሎችና አስተሳሰቦችን፣ አንዳንዴም በሕጋዊ መንገድ የተመዘገቡ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የራሱ አባላትን ጭምር ለማጥላላት የሚጠቀምባቸው ታፔላዎች ናቸው፡፡ በመሠረቱ ኢሕአዴግ ገነባሁት በሚለው የብሔር ብሔረሰቦችን የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት እስከ መገንጠል የተቀበለና የመድበለ ፓርቲ ሥርዓትን በሕገ መንግሥት ባረጋገጠ ሥርዓት ውስጥ፣ ሁለቱንም አስተሳሰቦች በሕጋዊ መንገድ አቅርቦ መታገል ሕገ መንግሥታዊ መብት እንጂ በሽብርተኝነት ለመፈረጅ የሚያስችል ሕጋዊ አግባብ የለም፡፡

በሌላ በኩል በማኅበራዊ ሚዲያም ሆነ በተለያዩ አካባቢዎች የተቃውሞ እንቅስቃሴ እያደረጉ ያሉት ወጣቶች ናቸው፡፡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከኢትዮጵያ ሕዝብ 60 በመቶው ከ30 ዓመት በታች የሚሆኑ ወጣቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ወጣቶች በኢሕአዴግ ዘመን የተወለዱ፣ ነፍስ ያወቁ፣ የተማሩና የጎረመሱ ናቸው፡፡ በአብዛኛው የፖለቲካ ንቃታቸውና አስተሳሰባቸው ከዚህ ሥርዓት ጋር በተያያዘ የተፈጠረ ነው፡፡  ትውልዱ በዕለት ተዕለት ኑሮው የሚያጋጥመውን የሥራ አጥነት፣ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት፣ የሕግ የበላይነት፣ የፖለቲካ ምኅዳር መጥበብ ጥያቄዎች ባቀረበ ቁጥር የከረሙ ፍረጃዎችን መለጠፍ ትውልዱን የተናቀ እንዲመስለው ከማድረግ የዘለለ ሚና አይኖረውም፡፡ እነዚህን አስተሳሰቦችም አምኖ ለተቀበለው ዜጋም ቢሆን ሐሳቦቹን በሐሳብና በፖለቲካ ትግል ለማሸነፍ መሞከር እንጂ፣ ዘለፋና ፍረጃ መደጋገም ጭራሽ ጽንፈኝነትን ያባብስ እንደሆነ እንጂ በምንም ተዓምር ብሔራዊ መግባባትን አይፈጥርም፡፡

የፖለቲካ ምኅዳር መጥበብ - ‘ምከረው ምከረው እምቢ ካለ መከራ ይምከረው’

ከ2007 ዓ.ም. ምርጫ በኋላ መንግሥት የፖለቲካ ምኅዳሩን የበለጠ ያጠበቡ ሕጎችንና ዕርምጃዎችን በመውሰድ አሥር ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የአገሪቱን የፓርላማ መቀመጫ መቶ በመቶ በመቆጣጠር ደካማ፣ ተፅዕኖ መፍጠር የማይችሉና በመዝናኛና በስፖርት ወሬዎች የተሞሉ ሚዲያዎችን፣ የተዳከሙ የሲቪል ማኅበራትንና እዚህ ግባ የሚባል ሚና የማይጫወቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲፈጠሩ በማድረግ በአገሪቱ ጉዳይ ራሱን ብቸኛ አሳቢና ፈጻሚ አድርጓል፡፡ ከወዳጅ መንግሥታት፣ ከምሁራንና ከራሱ የቀድሞ አባላትና አመራሮች ጭምር ይህ የፖለቲካ ምኅዳር መጥበብ በ21ኛው ክፍለ ዘመን የማይሠራና አገሪቱንም ወደ ከፋ አለመረጋጋት ሊያደርሳት እንደሚችል፣ የሌሎች አገሮችን ልምድ ጭምር በማንሳት ሲወተውቱና ሲመክሩ ቆይተዋል፡፡

ስለዚህ ጉዳይ ምርጫውን በዝረራ ባሸነፈ በማግሥቱ ከተነሱት ተቃውሞዎች ውጪ ማብራሪያ ማስፈለግ አልነበረበትም፡፡ በአገሪቱ ያሉ መሠረታዊ የፖለቲካ ጥያቄዎች የፖለቲካ ምኅዳሩ በትንሹ እንኳን ክፍት ቢሆን አሁን እየያዙ ካለው ጽንፈኝነትና ኢ-ምክንያታዊነት መዳን ይችሉ ነበር፡፡ ዜጎች በየጓዳው የሚያነሷቸው የፖለቲካ ጥያቄዎች በግልጽ ተቀምጠው ክርክር አይደረግባቸውም፡፡ ለምሳሌ በተቃውሞ እንቅስቃሴዎቹ ላይ ገኖ የወጣው አንዱ የፖለቲካ ጥያቄ  የሕወሓት የበላይነት ጥያቄ ነው፡፡ ይህ አስተሳሰብ በራሱ በድርጅቱ አባላትና ደጋፊዎች ጭምር ጠርቶ አለመውጣቱ፣ እንኳን በሕዝቡ ውስጥ በድርጅቱ ውስጥ እንኳን መተማመኛ እንዳልተደረሰበት በተቃውሞዎቹ ግልጽ ሆኗል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ አደገኛ አዝማሚያ እየያዘ ያለውን የአንድ ብሔር የበላይነት አለ የሚለው አመለካከት ያለቅጥ ተራግቦ ሳለ፣ በኢሕአዴግ ዘንድ ከተለመደው ፍረጃና ማጥላላት ውጪ ሐሳቡን ምክንያታዊ በሆነ መንገድ ሲከላከል አይታይም፡፡ እንዲያውም ብዙ ጊዜ ጉዳዩ እንዳለ እንኳን ለመቀበል የሚፈልግ አይመስልም፡፡

ምክንያታዊ ውይይትና ክርክር ሲጠፋ አሉባልታና የፈጠራ ወሬዎች ያለምንም ማረጋገጫ እንደ እውነት ይወሰዳሉ፡፡ በማኅበራዊ ሚዲያ አማካይነት ጽንፈኛና በስሜት የተሞሉ አስተሳሰቦች ምንም ሳይፈተኑና ሳይጣሩ በብዙ ሰዎች ዘንድ ይደርሳሉ፡፡ ይኼንን መዋጋት የሚቻለው ግልጽነትን በማስፈን፣ በብሔር ላይ የተመሠረቱ የጥቅምና የሙስና ትስስሮችን በመዋጋት፣ እንዲሁም ሚዲያው ሁኔታውን በግልጽ በማንሳት በማስረጃ በማስደገፍ ለማወያየት በመሞከር ነው፡፡ ኢሕአዴግ/መንግሥት የፖለቲካና ምክንያታዊነት ምኅዳሩን ያለቅጥ በማጥበብና የመንግሥት ሚዲያንም ለፕሮፓጋንዳ ሥራ በማዋል ኅብረተሰቡን ወይም በሶሻል ሚዲያ ያለምንም ተቆጣጣሪና ኃላፊነት ለሚተላለፉ መረጃዎች፣ አልያም በውጭ ላሉ ጽንፈኛ አመለካከቶችና አስተሳሰቦች ዳርገውታል፡፡

ማኅበራዊ ሚዲያው - ኢሕአዴግና መንግሥት የተሸነፉበት አውድማ  

በእኛ አገር ብቻ ሳይሆን በተለይም እንደኛ የሚስጥራዊነትና የቁጥጥር አስተዳደር መመሥረት ለሚፈልጉ መንግሥታት የዘመኑ ትልቁ ፈተና ቴክኖሎጂው የፈጠረው ማኅበራዊ ሚዲያ ይመስለኛል፡፡ በእኛ አገር እንደተደረገው አሳሪ ሕጎችን በማውጣት፣ ለነፃ ሚዲያ ምቹ ሁኔታን በመንፈግና ሚዲያው እውነተኛ ሕገ መንግሥታዊ ሚናውን እንዳይጫወት በማድረግ ሕዝብን ስብከት መሰል የልማት ወሬ የሚያወሩ የመንግሥት ሚዲያዎችን እንዲሰማ በማድረግ በአገሪቱ የሚናፈሰውን መረጃና የተለያየ አስተሳሰብ መቆጣጠር ይቻላል ተብሎ ሊታሰብ ይችላል፡፡ በእኔ እምነት የማኅበራዊ ሚዲያ መፈጠር ይኼንን አስተሳሰብ ምናልባትም ከመሠረቱ ለውጦታል፡፡ ማንም ሰው በእጁ በያዘው ሞባይል በመጠቀም መረጃ ይለዋወጣል፣ ሐሳብ ያንሸራሽራል፣ ይከራከራል፡፡ በተቃውሞዎቹ ወቅትም የታየው ይኼው ነው፡፡ መንግሥት የኢንተርኔት አገልግሎትን ለማቋረጥ ከፍተኛ ጥረት የሚያደርግ ቢሆንም በአገሪቱ ወረዳዎችና የገጠር አካባቢዎች ጭምር የተከናወኑ ነገሮች፣ የፀጥታ ኃይሎች የሚወስዷቸው ዕርምጃዎች በፎቶና በቪዲዮ ጭምር ታጅበው በደቂቃዎች ውስጥ ማኅበራዊ ሚዲያው ይለቀቃሉ፡፡

አመለካከትን በበጎም ሆነ በመጥፎ፣ በተለይም በዋኝነት ተጠቃሚ በሆኑ ወጣቶች ዘንድ ለማድረስ ከፍተኛ አቅም ባለው ማኅበራዊ ሚዲያ ኢሕአዴግና አባላቱ በመንግሥት ሚዲያ ነጋ ጠባ ከሚነገሩ ነገሮች ውጪ፣ እነዚህን አመለካከቶች ለመከላከልና መልስ ለመስጠት ሲጠቀሙበት አይታይም፡፡ ምሁራንና ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ምክንያታዊና ለአገሪቱ ወሳኝ የሆኑ ጉዳዮችን በማንሳትና በማወያየት አስተሳሰቦችን ለመቅረፅ ሲሞክሩ አይታይም፡፡

መሪ የሌለው ተቃውሞ እስከ መቼ?

በኦሮሚያም ሆነ በአማራ እየተጠሩ ያሉት ተቃውሞዎችና ሠልፎች በማኅበራዊ ሚዲያውና አክቲቪስቶች የሚስተባበሩ ይመስላሉ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በባህር ዳር ለመውሰድ ከሞከረው የማስተባበር ሚና ባሻገር በአገሪቱ ተመዝግበው እየተንሳቀሱ ያሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተቃውሞውን የማስተባበርና የመምራት ሚና ሲጫወቱ አይታይም፡፡ በአንዳንድ አገሮች እንደታየውም ሲቪል ማኅበራትና ሌሎች ማኅበረሰባዊ ቡድኖችም ይህንን ሚና ሲጫወቱ አይታዩም፡፡ መንግሥት ለመደራደርና በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ዕርምጃዎች ጥያቄዎቹን ለመመለስ የእውነት ፈቃደኛ ቢሆን እንኳን በተቃውሞ የተነሱ ጥያቄዎችን በደረጃ ዘርዝሮ፣ ለመደራደር የሚችለው የትኛው ቡድንና አካል እንደሆነ ለመለየት ያስቸግራል፡፡ የመንግሥት ሥልጣን ለመያዝ ተመዝግበን እንንቀሳቀሳለን የሚሉት ተቃዋሚ ፓርቲዎች እንኳን የመሪነት ሚናን ሊወስዱ በተቃውሞ እንቅስቃሴው ላይ በቂ ትንታኔ ሳይኖራቸው የተደበቁ ነው የሚመስሉት፡፡ በአንድም በሌላም መንገድ ጥያቄዎቹን ለማስተባበርና ሥርዓት ለማስያዝ ካልተሞከረ መቋጫ ለሌለው አላስፈላጊ መስዕዋትነት ከመዳረጉም ባሻገር፣ ከተቃውሞዎቹ የሚገኘውን የፖለቲካ ትርፍ በማሳጣት ኢሕአዴግ በራሱ ለመሻሻል ቃል ከመግባት ውጪ ተጨባጭ አንድምታ እንዳይኖራቸው ያደርጋል፡፡

የመንግሥት ምላሽ - ኃይል ኃይል አሁንም ኃይል

የፌደራል ሥርዓቱ ሊያጋጥሙት የሚችሉ ጥያቄዎች የሚመልስበት አግባብ በሕገ መንግሥት ተቀምጠው ሳለ፣ የኢሕአዴግ መንግሥት ላለፉት ዓመታት ችግሮችን በፓርቲና በፖለቲካ መስመሮች ለመፍታት በመሞክሩ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱ ሊያገኝ ይገባ የነበረው ልምድና ችሎታን አሳጥቶታል፡፡ በመሠረቱ በዴሞክራሲ መብቶች መረገጥና ዜጎች መብታቸውን በመጠየቃቸው ምክንያት በመታሰራቸውና በመገደላቸው ምክንያት ጫካ ገብቶ በትጥቅ ትግል ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈለ መንግሥት፣ በፀጥታ ኃይሎች ዕርምጃና ጥንካሬ ዘላቂ ሰላምን ፈጥሬ አገሪቷን አስተዳድራለሁ ብሎ ማሰቡ እጅግ አሳፋሪ ነው፡፡ የፖለቲካ ዋጋውም ለድርጅቱ ብቻ ሳይሆን ለአገሪቱም እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡

ሕገ መንግሥት ባለበት አገር የፀጥታ ኃይሎች የሚገዙበት የኃይል አጠቃቀም ሕግ ባለበት አገር፣ የአደጋ ጊዜ አዋጅ ባልታወጀበትና የለየለት ጦርነት በሌለበት ሁኔታ ማንም በሕገ መንግሥት እገዛለሁ የሚል አገር ዜጎቹን አንዱንም ቢሆን፣ በየመንገዱ መግደል፣ መደብደብ፣ ማሰርና ማሰቃየት የለበትም፡፡ በዚህ ዘመንም እንደዚህ እያደረጉ አይታወቅብኝም ብሎ ማሰብ ሞኝነት ነው፡፡ እነዚህ ሃይ ባይ የሌላቸው ዕርምጃዎች ብሶትን ከመጨመርና በዜጎች ዘንድ ከፍተኛ ቂም ከመፍጠር በዘለለ በማስፈራራት ተቃውሞዎቹን የማስቀረት አቅማቸው አናሳ መሆኑ፣ በኦሮሚያ ማስተር ፕላኑ ከተሰረዘ በኋላ ሠልፎቹ መቀጠላቸውና የፀጥታ ኃይሎች ያልተመጣጠነ ዕርምጃ እንደ አንድ ዋና ጥያቄ መነሳቱ ለዚህ አንዱ ማሳያ ነው፡፡ የዚህ ሁሉ ዜጋ ሕይወት አልፎ አንድም የፀጥታ አባል ተጠያቂ አለመደረጉ ሰብዓዊ መብቶችና ሕገ መንግሥቱ የፖለቲካ ሰነድ ከመሆን ባሻገር ለዜጎች ጥበቃ እንደማያደርጉ በማመላከት ዜጎች በሰላማዊ ትግል ተስፋ እንዲቆርጡ የሚያደርግ ነው፡፡ 

የጦርነት ነጋሪትና በጦርነት የማይፈታ ጥያቄ

መንግሥት በጉልበቱ በጣም በመተማመን ራሱን ብቻ እያዳመጠ ተቃውሞዎቹን፣ ሕዝቡንና ጥያቄውን ያነሱትን ዜጎች በማይመጥን ሁኔታና በጉልበት ለመመለስ የሚሞክር ከሆነ የትጥቅ ትግልን እንደ መፍትሔ የሚቆጥሩ ዜጎች ቁጥር ይጨምራል፡፡ የዴሞክራሲ ሥርዓትና ግንባታና በተቃውሞዎቹ የተነሱት ጥያቄዎች ጦርነትን በማሸነፍ ሊመለሱ እንደማይችሉ የእኛኑ አገርን ጨምሮ በብዙ አገሮች የታየ ነው፡፡ በእኔ እምነት አሁን አገራችን ባለችበት አቋም ወደ እርስ በርስ ጦርነት ውስጥ መግባት እንደ አማራጭ ከታየ ከዚያ የሚተርፍ አገር ይኖራል ብዬ አላስብም፡፡

በሌላ በኩል የመንግሥትን ባህሪ እየተረዱና እያወቁ፣ ፈረንጅ አገር የሚገኝ ኮምፒዩተራቸው ላይ ተቀምጠው አሁንም አሁንም ሠልፍ በመጥራትና በለው በለው በማለት የዜጎችን ክቡር ሕይወት አላስፈላጊ በሆነ መንገድ እንዲጠፋ ማድረግ፣ ከመንግሥት ባልተናነሰ ኃላፊነት ማጣት ነው፡፡ ያለምንም ማረጋገጫ ሕዝብን የሚያውክ፣ ሕዝብን በሕዝብ ላይ የሚያነሳሳ የጥላቻ አመለካካትን መንዛት አገሪቱ ለሁላችንም እንዳትሆን ከማድረግ የዘለለ እርባና እንደሌለው አለመረዳት ግዴለሽነት ነው፡፡

የፖለቲካው መንታ መንገድ

ኢሕአዴግ የሕዝብ ጥያቄና ብሶት መኖሩን እንደሚያምንና በቅርቡ ተሃድሶ መሰል እንቅስቃሴዎችን በማድረግ ራሱን እንደሚያስተካክል ለሕዝብ ገልጿል፡፡ ይሁንና አሁንም በዝግ ስብሰባና በድርጅታዊ መንገድ፣ እርስ በርስ በመገማገምና ጥቂት ሰዎችን ከሥልጣን በማንሳት ከሕዝብ የተነሳበትን ጥያቄ ለመፍታት የሚሞክር ከሆነ ከፍተኛ ስህተት ነው፡፡ የፖለቲካ ምኅዳሩ ጉዳይ ለኢሕአዴግ ብቻ ሳይሆን ለአገሪቱም እጅግ ወሳኝ ጥያቄ ሆኗል፡፡ የፌደራል ሥርዓቱ መጎልመስና ከሥርዓቱ የሚነሱ ጥያቄዎችን በሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት አግባብ መመለስ ወሳኝ የፖለቲካ ጥያቄ ሆኗል፡፡ ነፃና ሕገ መንግሥታዊ ሚናቸውን የሚወጡ የዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት መኖር፣ የተለያዩ አመለካከቶችን በግልጽነትና በምክንያታዊነት የሚያንሻራሽሩ ሚዲያዎች መፈጠር፣ ሙስናና በተለያየ መረብ የተሳሰሩ የጥቅም ትስስሮችን መዋጋት ለአገሪቱ ህልውና ወሳኝ ነው፡፡

ስለዚህም ኢሕአዴግ ጉዳዮቹን መመርመር ያለበት ሥርዓቱንና የልማታዊ መንግሥት አስተሳሰብን እየተገበረበት ያለበትን መንገድ በጥልቀት ከማየት ነው እንጂ፣ መልካም አስተዳደር ማስፈንና ሙስናን መዋጋት በሚሉ፣ ቢሳኩ እንኳን መሠረታዊ ችግሮቹን በማይፈቱ ዕርምጃዎች ከሆነ አገሪቱ ምናልባትም አሸናፊ ወደማይኖረው ብጥብጥ የማምራት ዕድሏ የሰፋ እንዳይሆን ያሰጋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆነ ድርጅቱ በተለያዩ አጋጣሚዎች ‘ራሳችንን መፈተሽና ማስተካከል አለብን’ የሚል ምክር የሚመስል ሐሳብ በመሰንዘር ችግሩን እንደማይፈቱት ይታወቃል፡፡ አገሪቱ የፖለቲካ ኃይሎች ይህንን የሕዝብ ተቃውሞ ከስሜታዊነትና ከማናለብኝነት ወጥተው አገርና ዜጎችን  ለዘለቄታው በሚጠቅም መልኩ ካልመሩት መንታው መንገድ ወዳልተፈለገ አቅጣጫ ሊወስደን እንደሚቻል ግልጽ ሊሆን ይገባል፡፡

ከአዘጋጁ፡-ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው ayteng1986@gmail.comማግኘት ይቻላል፡፡

 

Standard (Image)

‹‹አወቅሽ . . . አወቅሽ ሲሏት መጽሐፉን አጠበች››

$
0
0

 (ክፍል ሁለትና የመጨረሻው)

    በመሓሪ ይፍጠር

ውድ አንባቢያን በክፍል አንድ ጽሑፌ ላይ “ጆቤ” በሠራዊቱ ግንባታ ሰነድ ላይ ያነሷቸውን ሐሳቦች ከተጨባጭ ሰነዱ ጋር በማመሳከር ነጥቦቹ ትክክል አለመሆናቸውን ለማሳየት ሞክሬያለሁ። ሰውዬው ለማንሳት የሞከሯቸው ሌሎች ጉዳዩችንም እንዲህ ተመልክቻቸዋለሁ። መልካም ንባብ።  

ጡረተኛው ሜጄር ጄኔራል ሰነዱን አስመልክተው ያነሷቸው ሐሳቦች ለእሳቸው ፍጆታ በሚውል መልኩ ቀነጫጭበውና እውነት አስመስለው ለማቅረብ ሞክረዋል። ለዚህም “በእኛ ተጨባጭ ሁኔታ የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓታችን ደኅንነት መከላከል ማለትና የአገር ደኅንነት መከላከል ማለት በመሠረቱ አንድ ነው ማለት ይቻላል፤” የሚለውን አባባል ለማብራራት የተቀመጡትን ሐሳቦች ሆን ብለው ለመመልከት አልፈቀዱም ወይም ዓይተው እንዳላዩ አልፈዋቸዋል። ይሁንና እኔ ግን ሀቁን ለመግለጽ እሞክራለሁ። በማንኛውም አገር ውስጥ አገርን በመምራት ላይ የሚገኝ ኃይልን በታጠቀ ኃይል የመቀየር ተቃውሞ በሚያጋጥምበት ወቅት ሥርዓቱ ምንም ዓይነት ይሁን (ፊውዳላዊም ሆነ አብዮታዊ፣ ሊበራላዊ ሆነ ሃይማኖታዊ. . . ወዘተ) ሌላ ጉዳይ ሆኖ፣ ያ ሥርዓት ደኀንነቱን ለማስጠበቅ ሲል የመከላከያ ኃይሉን ተጠቅሞ ራሱን መከላከሉ የሚቀር አይሆንም። ይህ ደግሞ ከፓርቲው ውጪ ሆኖ አንድን ፓርቲ ወይም ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ከመጠበቅ አንፃር ሊገለጽ እንደሚችል፣ ይኼም የአገርን ደኅንነት መጠበቅ ማለት እንደሆነ መጽሐፉ ያስረዳል። እናስ ጡረተኛው ጄኔራል መኮንን ከቶ ምን እያሉን ይሆን?

ያም ሆነ ይህ ግን በቅድሚያ በመጸሐፉ ላይ የተጠቀሰው፣ “በእኛ ተጨባጭ ሁኔታ. . .” የሚለው አባባል ከአገራችን ነባራዊ ታሪክ እንዲሁም ፖለቲካል ኢኮኖሚ ሁኔታ አኳያ የተሳሰረ መሆኑን ግለሰቡ የሚዘነጉት አይመስለኝም። ይህ ማለት ደግሞ ባለፉት 25 ዓመታት በተከናወኑት አምስት አገራዊ ምርጫዎች መራጩ ሕዝብ እዚህ አገር ውስጥ የአውራ ፓርቲ ሥርዓት (Dominant Party System) ዕውን እንዲሆን ይሁንታውን ሰጥቷል። እንደሚታወቀው በአንድ አገር ውስጥ የአውራ ፓርቲ ሥርዓት አለ የሚባለው፣ ገዥው ፓርቲ ለብቻው ወይም በጥምረት (ተጣማሪው ፓርቲ ተመሳሳይ ፖሊሲን የሚከተል ከሆነ) ለረጅም ጊዜ መንግሥት ሆኖ የመሪነቱን ቦታ ሲይዝ ነው።

ይህ የፖለቲካ ሥርዓት ዓይነት የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት አካሄድን የሚከተል በመሆኑም፣ በውስጡ ያሉት ተቃዋሚ ፓርቲዎች በሕጋዊ መንገድ ተንቀሳቅሰውና ሐሳባቸውን በግልጽ አስረድተው በአገሪቱ ውስጥ በሚደረጉ ምርጫዎች ተወዳድረው የማሸነፍ ሕጋዊ መብት አላቸው። ሥርዓቱን ከሚያራምዱ አገሮች ውስጥ ጥቂቱን በማሳያ ምሳሌነት ብናነሳ እንኳን የናይጄሪያን፣ የሩዋንዳን፣ የኢኮቶሪያል ጊኒን፣ የደቡብ አፍሪካንና የጃፓንን አውራ ፓርቲዎች መጥቀስ የሚቻል ይመስለኛል። ይኼም የአውራ ፓርቲ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት በዓለም ላይ ያለና በርካታ አገሮች  የሚከተሉት መሆኑን ያሳያል። የአገራችንም የአውራ ፓርቲ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ከዚሁ ነባራዊ ሁኔታ ተለይቶ የሚታይ አይደለም።

እናም በእኔ እምነት ይህ የአውራ ፓርቲ ሥርዓት በሕዝቡ ምርጫ ዕውን የሆነበት ተጨባጭ ምክንያት፣ የሕዝቡን ቀልብ መሳብ የቻለ ወይም ለአቅመ ተቃዋሚነት የደረሰ ፓርቲ ባለመኖሩ ነው። በሌላ አገላለጽ ሕዝቡ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓቱ ያመጣውን የሰላም፣ የልማትና የዴሞክራሲ ግንባታን አካሄድን መተኪያ በሌለው አማራጭነት መቀበሉና ተቃዋሚዎችም ለይስሙላ በሕገ መንግሥቱ እየማሉ፣ በሌላ በኩል ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመናድ በመሞከራቸው በእነሱ እምነት ማጣቱን የሚያሳይ ነው። እናም እንዲህ ዓይነቱ ተጨባጭ የሕዝብ ፍላጎት ባለበት አገር ውስጥ፣ የአገሪቱ ዘብ የሆነው የመከላከያ ኃይል ከገዥው ፓርቲ ርዕዮተ ዓለም ተነጥሎ እንደምን ሊገነባ እንደሚችል የሚያውቁት እሳቸው ብቻ ይመስሉኛል።

ምንም እንኳን እሳቸው ”የምንገነባው መከላከያ ኃይል ዓላማው የሥርዓታችንን ደኅንነት መጠበቅ ነው ሲባል የሚገነባውና የሚመራው በሥርዓቱ መሪ የሆነው አካል ብቻ ነው፤” የሚለውን የመጽሐፉን አባባል በሚያስገርም ሁኔታ “በጭንቀት፣ በልመና የተደጋገመ ፀሎት አይሉት ምህላ. . .” በማለት ሠራዊቱ የሚገነባው ለጥቂት ግለሰቦች ጥቅም ሲባል እንደሆነ አስመስለው ለመግለጽ ቢሞክሩም፣ ሀቁ ግን አሁንም በመጽሐፉ ላይ የተጠቀሰውን ማብራሪያ ሆን ብለው በመዝለል እርሳቸው ካላቸው ፍላጎት በመነሳት ያልተገባ ስያሜ ለሠራዊቱ ለመስጠት ያለመ ይመስለኛል። አዎ! “ጆቤ” ከጠቀሱት አባባል በታች ሰነዱ ገጽ 28 ላይ የመከላከያ ኃይሉን የመምራት፣ የመገንባትና የማሰማራት ሁኔታዎችን ከማንም ጋር በመከፋፈል ሊከናወን እንደማይችልና እንዲህ ዓይነቱ አሠራር በሌሎች ሥርዓቶችም ገቢራዊ እንደሚሆን ያብራራል። አንድ በሥልጣን ላይ የሚገኝ አካል መሪነቱን ከሌሎች ጋር የማይጋራበት ወይም የማይከፋፈልበት ሁኔታዎችና አጋጣሚዎች ብዙ ቢሆኑም፣ ወትሮና በማንኛውም ጊዜ የአመራሩን ጉዳይ በተመለከተ ወደ ድርድር የማያቀርበው ነገር ቢኖር የሥርዓቱ የመጨረሻ ምሽግ የሆነው የመከላከያ ኃይል እንደሆነ መጽሐፉ በግልጽ ያስረዳል።

እርግጥም ሌላው ቀርቶ አድጋለች በምትባለው አሜሪካ ውስጥም ቢሆን የሚገነባ ሠራዊት እንኳን ሳይቀር፣ የሊብራሊዝም ቀኖናን ከልጅነቱ ጀምሮ በተረትና ምሳሌ መጻሕፍት ላይ ሳይቀር እየተነገረውና እየተማረ ያደገ መሆኑን “ጆቤ” የሚስቱት አይመስለኝም። ካደገም በኋላ ቢሆን ሠራዊት ውስጥ ገብቶ “መኮንን” (Officer) መሆን የሚችለው ለሥርዓቱ ካለው ቀረቤታና ታማኝነት አኳያ እየተመዘነ ነው። ይህ ካልሆነና ግለሰቡ በሥርዓቱ ላይ በቂ ዕውቀት ከሌለው ከ“ባለሌላ ማዕረግተኞች” (Non-Commissioned Officers - NCO’s) ምድብ ይሆንና ወሳኝ በሆኑ የመሪነት ጉዳዩች ውስጥ እንዳይገባ ይደረጋል። ሊብራል ሥርዓቱን የሚቃወም ከሆነ ደግሞ ወደ ሠራዊቱ ሊቀላቀል አይችልም። እናስ ለጡረተኛው ሜጄር ጄኔራል የእኛ አገሩ ሁኔታ አዲስ መስሎ የታያቸው ከምን መነሻ በመነጨ ይሆን? በእኔ እምነት እንዲያው ዝም ብለው በደፈናው የሠራዊቱን የግንባታ መስመር በማጣጣል ጥላሸት ለመቀባት አስበው ይመስለኛል።  

እርግጥም ይህ የእሳቸው ጥላሸት የመቀባት ፍላጎት “መጽሐፉ ሕገ መንግሥታችንን በውል መጥቀስ የጀመረው በገጽ 87 ነው” እስከሚለው የቅጥፈት ድርሰታቸው ድረስ የሚዘልቅ ነው። ለነገሩ ማንም ሰው ያንን መጽሐፍ ገለጥ ቢያደርገው ሩቅ ሳይሄድ በገጽ 23 ላይ ሕገ መንግሥቱን ቢያንስ ሁለቴ ተጠቅሶ ያገኘዋል። እናም እኔ ‘ጡረተኛው ሜጄር ጄኔራል ሆይ! ለምን ይዋሻል?’ ብዬ ልጠይቃቸው እወዳለሁ፡፡ ዕውን የሠራዊቱን ሕገ መንግሥታዊ ፅናት በሐሰት የገጽ ቁጥርን በመቀያየር ጭምር ኢሕገ መንግሥታዊ ማድረግ ይቻላልን? መቼም “ጆቤ” የሕግ ምሁር እንደመሆናቸው መጠን እንበልና አንድ ሰው እንዲከሰስ የሚመለከተው አንቀጽ ቁጥር 23 ሆኖ ሳለ፣ በአንቀጽ ቁጥር 87 ሊወነጀል እንደማይችል ከእኔ በላይ ስለሚያውቁ ስለቁጥር ምንነትና መዘበራረቅ ልነግራቸው አልሻም፡፡ እንዲህ ዓይነቱን የውሸት የቁጥር ጨዋታን ለምን ለመጫወት እንደሞከሩ የሚያውቁት እሳቸው ናቸውና።

በዚህ ሁኔታ የሠራዊቱን የግንባታ ሰነድ ቁጥሩን ሳይቀር በሐሰት ያዘበራረቁት “ጆቤ” ዝቅ ብለውም “መዘባረቁን በማያሻማ ሁኔታ እየቀጠለ (ሰነዱን ማለታቸው ነው) ‘ኢሕአዴግ ከሌለ ይህቺ አገር የለችም የሚለውን አባባል ሲያመላልሰው ይታያል’ ይሉናል። እኔ ግን እርሳቸው እንዳሉት አይመስለኝም። እናም አባባሉን ግን ከግሌ እምነት በመነሳት ለማብራራት እሞክራለሁ፡፡ ጡረተኛው ሜጄር ጄኔራል አውቀው የዘለሉትን የመጽሐፉን ክፍሎች በማጣቀስ ጭምር።

በእኔ እምነት በመንግሥት የተዘጋጀው ይህ ሰነድ ትክክል ይመስለኛል። ምክንያቱም ገዥው ፓርቲ ባይኖር ኖሮ የዛሬ 25 ዓመት ገደማ ታጥቀው የነበሩ 17 የሚጠጉ የተለያዩ ብሔር ተኮር ድርጅቶችን በአግባቡ ማስተናገድ ባልተቻለ ነበር። በወቅቱ ገዥው ፓርቲ በአገሪቱ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ሕግን ተከትሎ ብርቱ ተግባር ባያከናውን ኖሮ፣ አንዳንድ ሟርተኞች “ኢትዮጵያ ትበታተናለች፣ አበቃላት” በማለት የተነበዩት ነገር ዕውን በሆነ ነበር። ምሥጋና ለገዥው ፓርቲ ይሁንና ይህ የመበተን አደጋ ተፈጻሚ አልሆነም። የዛሬን አያድርገውና ራሳቸው “ጆቤ”ም ቢሆኑ ሥልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት (ከዛሬ 15 ዓመታት በፊት ማለቴ ነው) ይህን ዕውነታ ይጋሩት ነበር፡፡ አዲስ ኒዮሊበራላዊ ካባን ተከናንበው ብቅ ካሉበት ከተሃድሶው መስመር በፊት። ታዲያ ምነዋ ዛሬ ላይ ይህን ዕውነታ ከ15 ዓመት በኋላ በተገለበጠ መነጽር ለመመልከት ፈለጉ? ሕገ መንግሥቱን ስለተፃረሩ ከኃላፊነታቸው በመነሳታቸው ምክንያት ነው ወይስ በሌላ? እርግጥ ምላሹ የእሳቸው እንጂ የእኔ አይደለም።

“ጆቤ” ከመጸሐፉ ለመጥቀስ አልፈለጉም እንጂ ሰነዱ ዕውነታውን በራሱ መንገድ ገልጾታል። ይኼውም ሥርዓቱ ከሌለ ሕዝቦች ለዘመናት ሲጠይቁ የነበሩትና በአሁኑ ወቅት ዕውን እያደረጉ ያሉት ፈጣንና ቀጣይነት ያለው የምጣኔ ሀብት ልማት፣ የማኅበራዊ ዕድገት እንዲሁም ዴሞክራሲያዊ አንድነትና ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነት. . . ወዘተ የመሳሰሉ ጉዳዩች ሊኖሩ እንደማይችሉ ያትታል። እነዚህ ጉዳዩች ከሌሉ ደግሞ አገሪቱ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ ተከስቶ ወደለየለት ብተና ማምራታችን እንደማይቀርም እንዲሁ።

እርግጥም እዚህ አገር ውስጥ የተፈጠሩት የሰላም፣ የልማትና የዴሞክራሲ እመርታዎች ሥርዓቱን የሚመራው ገዥ ፓርቲ በተከተለው ትክክለኛ የዕድገት መስመር የተገኙ ናቸው። ሥርዓቱን የሚቃወሙ ወገኖች ካሉ እየተቃወሙ ያሉት ይህን ሁለንተናዊ የዕድገት ጎዳና ነው። ይህ የዕድገት መስመር ከተቋረጠ ደግሞ ከፌዴራላዊ ሥርዓቱ አኳያ ገና ጀማሪ የሆንባቸውና ካለፉት ሥርዓቶች ሲንከባለሉ የመጡት የገዥና ተገዥ ስንኩል አስተሳሰቦች የተፈጠረውን ዴሞክራሲያዊ አንድነትና ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነት በመሸርሸር፣ አገራችንን የሁከትና የብጥብጥ አውድማ ማድረጋቸው የሚቀር አይመስለኝም። በቅርቡ በኦሮሚያና በጎንደር አንዳንድ አካባቢዎች የታዩትና አገራችን እንድትበተን በሚሹ የውጭ ኃይሎች እንዲሁም የውስጥ ጀሌዎቻቸው አማካይነት የተቀነባበሩት የፀረ ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነትና የሕገ ወጥነት ዝንባሌዎች የዚሁ ሀቅ ጥሩ ማሳያዎች ይመስሉኛል።

እናም በእኔ እምነት ይህን ችግር መፍታት የሚቻለው በሕገ መንግሥቱ መሠረት ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነትንና አንድነትን ዕውን ያደረገው፣ እንዲሁም ሕዝቦችን አስተባብሮ ዛሬ ለደረስንበት የህዳሴ ጉዞ ያበቃን ገዥው ፓርቲና እርሱ የሚከተለው ርዕዩተ ዓለም ብቻ እንጂ፣ እነ “ጆቤ” የሚያቀነቅኑለትና ከአገራችን ታሪክና ተጨባጭ ሁኔታ ጋር አብሮ የማይሄደው እንዲሁም ጥቂቶችን ቱጃር አድርጎ ሚሊዮኖችን በድህነት አረንቋ ውስጥ የዘፈቀው የኒዮሊበራሊዝም ቀኖና አይደለም። ይህ የእኔ እምነት ነው፣ የጡረተኛው ሜጄር ጄኔራል አስተሳሰብ ደግሞ ሌላ ሊሆን ይችላል፣ መብታቸው ነው።

አዎ! ከዛሬ 25 ዓመት በፊት አገራችንን ከብተና ያደነ መስመር ዛሬም ሆነ ነገ ከሚጋረጡብን ማናቸውም አደጋዎች የሚያድነን ገዥው ፓርቲ ብቻ መሆኑን አስረግጨ መግለጽ እወዳለሁ። ኧረ ለመሆኑ እውነት እውነቱን እንነጋገር ከተባለ ኢሕአዴግ ባይኖር ኖሮ ከቶ የትኛው ኃይል ነው የዚህን አገር ችግር በሰከነ ሁኔታ ተሸክሞ ሊሄድ የሚችለው? የትኛውስ አቅም ያለው ፓርቲ ነው እሱን ሊተካው የሚችለው?. . . ለምን ሀቁን እያወቅን “ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ” የሚሉት ይትብሃል ዓይነት እንደባበቃለን?. . . ያም ሆነ ይህ ግን እዚህ አገር ውስጥ በመተግበር ላይ ያለውን ሥርዓት ያመጣው ገዥው ፓርቲ እንደመሆኑ መጠን፣ ሥርዓቱን የመጠበቅ ኃላፊነት ያለበት መከላከያ ሠራዊቱም ከዚህ አኳያ ዕውነታውን ቢገነዘበው ምንም ዓይነት ችግር ሊኖረው የሚችል አይመስለኝም፡፡ እየተነገረ ያለው ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ከፓርቲ ወገንተኝነት ውጪ ስለመጠበቅና ስለመከላከል ጉዳይ ነውና።

ጡረተኛው ሜጄር ጄኔራል በሰነዱ ላይ፣ “እኛ ብለው የሚጽፉ አመራሮች በአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ሽፋን እኛን አገልግሉ ከሚል ውጪ ያስቀመጡት የተለዩ የግንባታ ዓላማዎችና አቅጣጫዎች የሉም፤” ይላሉ። ለጥቀውም፣ “እኛ” ማነው?›› ብለው ይጠይቁና ወረድ ብለው ደግሞ፣  “በሠራዊት ግንባታ ላይ ያለው ‘እኛ’ አድኃሪ ነው፣ ፀረ ዴሞክራቲክ ነው፣ ፀረ ሕገ መንግሥት ነው፤” የሚል ብያኔ ራሳቸው ላነሱት ጥያቄ ምላሽ ራሳቸው ይሰጣሉ። እንዲህ ዓይነት ክስተት ሲያጋጥም ይመስለኛል የአገራችን አርሶ አደር “አንቺው ታመጪው፣ አንቺው ታሮጪው” የሚለው። ለመሆኑ “እኛ” ማለት ችግሩ ምንድነው? እርግጥ “እኛ”ን “ጆቤ” አያውቁትም ብዬ አላስብም። አዎ! መጽሐፉን ያዘጋጀው መንግሥት “እኛ” ሲል ጥቂቶችን ሳይሆን በአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ መስመር የሚያምነውን ማንኛውንም የኅብረተሰብ ክፍል ማለቱ ይመስለኛል፡፡ በተለይም የተሃድሶውን መስመር ለማሳለጥ የተሠለፈውንና ከታች እስከ ላይ ያለውን የኅብተረሰብ ክፍል። “እነሱ” ከተባለ ደግሞ ምናልባትም የተሃድሶውን መስመር ለማደናቀፍ የተሠለፉት እነ “ጆቤ” እና ጥቂት የሐሳብ አጋሮቻቸው ሊሆኑ የማይችሉበት ምክንያት ያለ አይመስለኝም። እናም የሰነዱ ባለቤት የሆነው መንግሥት “እኛ. . . እኛ ነን፤ ‘እናንተ’ ደግሞ እናንተ ናችሁ፤” ሊላቸው ቢችል ምላሻቸው ምን ሊሆን እንደሚችል አላውቅም። 

ያም ሆኖ ግን የ“እኛ” እና “የእነሱን” የቃላትና የተግባር አሠላለፍን እዚህ ላይ ልግታውና ጡረተኛው ሜጄር ጄኔራል፣ “እኛ የሚለው አድኃሪ፣ ፀረ ዴሞክራቲክና ፀረ ሕገ መንግሥት ነው፤” በማለት ስለገለጹት የተሳሳተ ምልከታ ላምራ። እርግጥ “እኛ” ማለት በዋነኛነት ከተሃድሶው መስመር ወዲህ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ መስመሩን በመከተልና እርሱን የመጨረሻ አማራጭ በማድረግ ለአገሩ ሁለንተናዊ ዕድገት ደፋ ቀና ብሎ ራሱን በየደረጃው በመጥቀም አገሪቱን ያሳደገ አብዛኛው ሕዝብ መሆኑን ከተግባባን ዘንዳ፣ ይህ ሕዝብና አመራሩ “ጆቤ” እንደሚሉት ከቶም አድኃሪ ሊሆን አይችልም። ይህ ሉዓላዊ ሥልጣኑን ተጠቅሞ በሕገ መንግሥቱ መሠረት አብዮታዊ ዴሞክራሲን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በካርዱ የመረጠ የተሃድሶው መስመር ሕዝብ ፀረ ዴሞክራቲክና ፀረ ሕገ መንግሥት ተብሎም ሊፈረጅ አይችልም። እንዲህ ዓይነቱ ጥቅልና ተገቢ ያልሆነ ፍረጃ አንድም እዚህ አገር ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ጉዳይ ያለመገንዘብ፣ ሁለትም አመራሩን እንኳን ብንተወው ሕዝቡን መናቅ ከፍ ሲል ደግሞ በሕገ መንግሥቱ ላይ መዘባበት ይመስለኛል። ይህ ሀቅም በእኔ እምነት “እነርሱ” ወደሚለውና ተሃድሶውን ለማደናቀፍ ወደ ተሠለፉት ኃይሎች የሚወስደን ይመስለኛል። እነ “ጆቤ”ን ያንጠባጠበው የተሃድሶው ባቡር ለውጥና ዕድገት ፈላጊውን የአገራችንን ታታሪ ሕዝብ አሳፍሮ ተጠቃሽ የሚሆን ምጣኔ ሀብታዊ ዕድገትን ያስመዘገበ፣ ዴሞክራሲ እንደ ሸቀጥ ከውጭ የሚገባ ቁሳቁስ አለመሆኑን ተገንዝቦ ከአገሩ ተጨባጭ ሁኔታ አኳያ ዴሞክራሲውን የቀመረ፣ በአገር ውስጥ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በመጠበቅ አስተማማኝ ሰላምን ከመፍጠር ባሻገር በዓለም አቀፍ ደረጃ ከበሬታን ያገኘና ለጎረቤቶቹ ጭምር ቤዛ እየሆነ ያለን ሠራዊት የገነባ ሕዝብ ነው? ወይስ ከዚህ በተቃራኒ የተሠለፉት እነ “እነሱ” ናቸው በአድኃሪነት፣ በፀረ ዴሞክራቲክና በፀረ ሕገ መንግሥትነት መፈረጅ የሚኖርባቸው? መልሱን ለዚህ ጽሑፍ አንባቢያን እተወዋለሁ። አንድ ጉዳይ ግን ለመግለጽ ፈለግሁ። የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት ገና በመግቢያው ላይ ሲጀምር “እኛ. . .” ብሎ ነው። ይህ ማለት ደግሞ የአገሪቱን ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እንደሆነ ይጠፋዎታል ብዬ አልገምትም። እናም ሰነዱን በኢሕገ መንግሥታዊነት እየተቹ መልሰው ራስዎ ሕገ መንግሥቱን እየተቃረኑ አይመስልዎትምን?

ጡረተኛው ሜጄር ጄኔራል በሰነዱ ላይ ያሉት ጉዳዩች በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይና የደኅንነት ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይም የተቀመጡ መሆናቸውን ገልጸዋል። ሆኖም ያ ሰነድ በአደባባይ ለሕዝብ ሠራዊቱን፣ “የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ወይም የኢሕአዴግ የመጨረሻ መከላከያ ምሽግ ነው አይልም፤” የሚል የመቃወሚያ ሐሳብ በማንሳት “ለምን?” ሲሉ ይጠይቃሉ። ይህ ጥያቄያቸው ሁለት ጉዳዮችን የያዘ ነው። አንደኛው የሠራዊቱ የግንባታ ሰነድ በድብቅ ለሠራዊቱ የተዘጋጀ ማስመሰል ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በአገራዊ ስትራቴጂና በአንድ ተቋም መመርያ መካከል ያለውን ልዩነት ሆን ብሎ ለማምታታት መፈለግ ነው። ይሁንና “የሠራዊት ግንባታ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ” የሚለው ሰነድ በሕገ መንግሥቱ መሠረት የተዘጋጀና ማንኛውም አካል በቀላሉ ሊያገኘው የሚችል ነው። ለዚህም እኔ ራሴ እማኝ መሆን እችላለሁ። አንድ መከላከያ ውስጥ የማውቀውን ወዳጄን ‘መጽሐፉን ማንበብ ስለምፈልግ ወታደራዊ ሚስጥር ከሌለበት አምጣልኝ’ ብዬ ስጠይቀው ሰነዱን እጄ ላይ ለማስገባት የሁለት ሰዓት ጊዜ እንኳን አልፈጀብኝም። እርግጥም መጽሐፉ የተደበቀ ነገር የሌለው በመሆኑ በእጅ ለማስገባት ይህን ያህል ቀላል ነው።

ፖሊሲንና ስትራቴጂን ከአንድ መንግሥታዊ ተቋም መመርያ ጋር ሆን ብሎ ለማጣረስ በጡረተኛው ጄኔራል መኮንን የተደረገው ጥረትም ግርምትን ያጭራል። እርግጥ እርሳቸው ስለ ስትራቴጂና መመርያ ዕውቀት የላቸውም ባልልም፣ ፖሊሲና ስትራቴጂ አንድን ዓላማ ለማሳካት ስለአጠቃላይ ጉዳይ ምሥል የማስያዝና በአጠቃላዩ ውስጥ ያሉት ክፍልፋዩች የተተለመውን ዓላማ ለማሳከት እንዴት እንደሚዛመዱ የሚያሳይ ጥቅል አቀራረብ ነው። በተለይም ስትራቴጂ በማንኛውም ጊዜ የሚቀየር አይደለም። ለስትራቴጂው መነሻ የሆኑት ጉዳዩች ወይም የስትራቴጂው ዓላማዎች ሲቀየሩ ስትራቴጂውም አብሮ ይለወጣል። የውጭ ጉዳይና የደኅንነት ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይም ከዚሁ አኳያ የመከላከያ ጉዳዩች በጥቅል በተቀመጡ ሐሳቦች ተገልጸዋል። ይህ ማለት ግን ተቋሙ በመመርያነት የሚያወጣቸው ዝርዝር ጉዳዩችን ፖሊሲውና ስትራቴጂው ይመለከተዋል ማለት አይደለም። እናም በሰነዱ ላይ ስለአብዮታዊ ዴሞክራሲ ባይገለጽም፣ መንግሥት በተቋሙ ዝርዝር አሠራር ውስጥ እንዲሠፍር ማድረጉ ተገቢ ይመስለኛል። ጥቅል ጉዳዩችን በሚይዘው ፖሊሲና ስትራቴጂ ውስጥ ሁሉንም ነገር ዘርዝሮ ማስገባት አይቻልምና።      

“ጆቤ” በሚያስገርም ሁኔታ “ከሕገ መንግሥቱ ጋር ይጋጫል፤” በማለት ያልተገባ ስም ሰጥተውት “ከሥራ ይታገድ” የሚል “ብይን” እንደ ዳኛ ያስተላለፉበት ሰነድ፣ እሳቸው ያልጠቀሷቸውን የሠራዊቱን ወታደራዊ ግንባታ እጅግ በሚበዙት ገጾቹ  ይተነትናል። ከእዚህ መካከል መጽሐፉ ጦርነት የፖለቲካ አንድ ገጽታና ተቀጥያ መሆኑን፣ ስለመከላከያ አቅም በተለይም ስለጦርነት አቅሞች ምንነት፣ ኢኮኖሚ የመከላከያን አቅም ለማጠናከር ወሳኝ ጉዳይ ስለመሆኑ፣ ስለወታደራዊ ግንባታ ምንነት፣ መነሻና አፈጻጸም እንዲሁም በአነስተኛ ወጪ ጠንካራ የመከላከያ አቅምን ስለመገንባት ብሎም በመከላከያ ግንባታና በኢኮኖሚ ልማት መካከል ስላለው መደጋገፍ ከወቅቱ የዓለም ተጨባጭ ሁኔታ ጋር እያስተሳሰረ በሳይንሳዊ መንገድ የሚተነትን ነው። እናም ጡረተኛው ሜጄር ጄኔራል “ከሥራ ይወገድ” ያሉት ሰነድ እነዚህን ወታደራዊ ሳይንሳዊ ትንታኔዎችን ጭምር የያዘ ነው። እርግጥ ሰውዬው ምን እያሉን ነው?. . . አንድ ስለ “ደርግ መጣ” አስተያየት የሚሰጥ ሰው ማንኛውንም ነገር “ይወገድ” የሚል ከሆነስ ራሱ ስለ ደርግነት ማቀንቀን አይሆንበትምን?

በመጨረሻም ጡረተኛው ሜጄር ጄኔራል “ከሥራ ይወገድ” በማለት ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽፈው በመገናኛ ብዙኃን ይፋ ያደረጉት የሠራዊቱ የግንባታ ሰነድን የተመለከተው ደብዳቤያቸው በግብዓትነት የሚያገለግል ይመስለኛል። ግብዓትነቱ ግን ደብዳቤው እንደሚለው ሰነዱ ከሕገ መንግሥቱ ጋር በመጋጨቱ ዳግም እንዲታይ አይደለም፡፡ ቀደም ሲል ባቀረብኳቸው ተጨባጭ ማስረጃዎች ሰነዱ ሕገ መንግሥቱን የሚደግፍ እንጂ የሚቃረን አይደለምና። እናም ግብዓትነቱ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እሳቸው ለሚመሩት ድርጅትና አገር ጭምር ነው። ይኼውም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ ለመገናኛ ብዙኃን ለተሃድሶው መስመር እንቅፋት የሆኑ ጉዳዩችን ለመለየት ድርጅታቸው ሰፊ ውይይት ለማድረግ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ለገለጹበት አግባብ፡፡ የተሃድሶው መስመር ያንጠባጠባቸው ወገኖችም የተገኘውን አጋጣሚ ሁሉ በመጠቀም ሳይታክቱ በሚዲያ የሚለቋቸው አደናጋሪና ጥላሸት ቀቢ ጽሑፎች እስከ የት ድረስ ሊጓዙ እንደሚችሉ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳያቸው ይመስለኛል።

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው yimehari@yahoo.comማግኘት ይቻላል፡፡ 

 

 

 

 

Standard (Image)

ኢሕአዴግ ይፍረስ ወይስ ይታደስ?

$
0
0

በሊሕ ላማ

ጊዜው ጊዜ የሚሰጥ አይደለም፡፡ የሚገመትም አይደለም፡፡ በፍጹም ስለነገው ማወቅ አይቻልም፡፡ እናም ኢሕአዴግ ከፊት ለፊቱ ሁለት ወፍራም አማራጮች ተጥደውበታል፣ መፍረስ ወይም መታደስ፡፡ 17 ዓመታትን በበረሃ ከርሞ ሦስት አሠርታት ለሚጠጋ ጊዜ የቤተ መንግሥትን ጥቅም ያወቀ ድርጅት መፍረስን ይመርጣል ብሎ ማሰብ ከባድ ነው፡፡ ስለዚህ ምርጫው መታደስ የሚለው ይሆናል ማለት ነው፡፡ በእርግጥ መታደስም ቀላል አይደለም፡፡ የግንባሩ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴና ምክር ቤቱ ባወጣው መግለጫ ይህንን ሊያደርግ እንደሚችል በገደምዳሜ ተናግሯል፡፡ ‹‹ያለፉትን አሥራ አምስት ዓመታት (ከ1993 ዓ.ም. ተሃድሶ ወዲህ ያለውን ጊዜ ማለቱ ነው) ውጤትና ውድቀት በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል›› ማለት፣ በሌላ ቋንቋ ሌላ ተሃድሶ ሊያደርግ ነው የሚል ትርጉም እንዳለው የሚጠቁም ነው፡፡

ጥያቄዎቹ ‹‹በእርግጥ የአሁኑ ኢሕአዴግ ግልብጥብጥ ያለ ተሃድሶ ለማድረግ ወኔው አለው ወይ? ተሃድሶ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮችስ ምን ምን ናቸው? ይህንን ለማድረግ የሚያስችልና ተሃድሶውን የሚቀበል ግለሰብ ወይም ቡድን አለ ወይ?›› የሚሉ ይሆናሉ፡፡ ድርጅቱ ‹‹እኔ የራሴን ከራሴ እጀምራለሁ፣ ሥራ አስፈጻሚው ውስጥ በሥልጣን መባለግ አለ ይህንን አፀዳለሁ፣ ሥልጣንን የግል ጥቅም ማበልፀጊያ ያደረጉ ሰዎች በዝተውብኛል፣ እናም ሕዝብ ከጎኔ ይቁም፣ እኔም ራሴን አርማለሁ…›› ሲል በአደባባይ ንስሀ ገብቷል፡፡ እንደተባለው ግንባሩ መፍረስን የማይመርጥና ለመታደስ ከተዘጋጀ ቀላል የማይባሉ ወጥመዶች አሉበት፡፡ ወጥመዶቹ ወይ ይይዙታል ወይ እሱ ራሱ አስቀድሞ ይይዛቸዋል፡፡

ኢሕአዴግ ምን ዓይነት ተሃድሶ ያድርግ?

ፖለቲካዊ ተሃድሶ

በዚህ ወር ሁለተኛ አጋማሽ ላይ የወጣው የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ መግለጫ ስለፖለቲካዊ ተሃድሶ፣ ስለፖሊሲ ለውጥና ተያያዥ ጉዳዮች አያወራም፡፡ ይልቁንም ከ1993 ዓ.ም. ወዲህ ስኬታማ ፖሊሲዎቹ ያጎናፀፉትን ድል ይተርካል፡፡ ይኼ ምናልባት ለፖለቲካዊ ለውጥ አለመዘጋጀቱን የሚጠቁም ሊሆን ይችላል፡፡ ግን ይህንን ዓይነት ተሃድሶ ያላደረገ ኢሕአዴግ ከሞቱት በላይ ከቆሙት በታች መሆኑ የማይቀር ነው፡፡ በግልጽ ቋንቋ ፖለቲካዊ ተሃድሶ ያስፈልጋል፡፡ ፖለቲካዊ ተሃድሶ ሲባል ከስሙ ይጀምራል፡፡ ኢሕአዴግ የሚለው ሶሻሊስታዊ ስያሜ፣ ካፒታሊስት ነኝ ለሚል ድርጅት አይሆንም፡፡ ይህ ድርጅት እስካሁን አለመዋሀዱም ሆነ ፓርቲ አለመሆኑ ይዞት የመጣው ጣጣ ቀላል አይደለም፡፡ በ1980ዎቹ የመጀመሪያ ዓመታት ሕወሓትና ኢሕዴን ጥምረት የመሠረቱት ሥልታዊ በሆነ ምክንያት ነበር፡፡ ደርግን በጋራ ለመጣል!! ይህ ሥልት ግን ከሥልትም አልፎ ወደ ስትራቴጂካዊነትም አድጎ ዛሬም ድረስ አለ፡፡

ቀድሞ ነገር ፓርቲዎች ጥምረት የሚመሠርቱት የተለያየ ግን ለመታረቅ የማያስቸግር ርዕዮተ ዓለም ሲኖራቸው፣ በነጠላ ሥልጣን ለመያዝ የሚያስችል መተማመኛ ድምፅ ሲያጡ፣ ወዘተ. ነው፡፡ ኢሕአዴግ በተባለ ጃንጥላ ሥር ያሉ አራት ድርጅቶች ግን ቅንጣት ያህል የመርህ፣ የፖሊሲ፣ የርዕዮተ ዓለም ልዩነት ሳይኖራቸው ዛሬም በጥምረት ግንባር ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ የሕወሓትን ፖለቲካዊ ፍልስፍና ከብአዴን፣ የኦሕዴድን ከደኢሕዴን በአጠቃላይ አንዱ ከሌላው ያለውን ኅልዮት ለይቶ ማብራራት በማይቻልበት ሁናቴ ዛሬም በጥምረት ውስጥ ሆኖ ኢሕአዴግ መባሉ አስገራሚ ነው፡፡ እናም ግንባሩን አፍርሶ ከጥምረት ወደ ውህደት ማምጣት ድርጅቱን ከተጋረጡበት ፈተናዎች ሁሉ ለማዳን የሚያስችል የመጀመሪያ ደረጃ ሕክምና ነው፡፡ ከዚያም ኢሕአዴግ የግንባር ባርኔጣውን አውልቆ ፓርቲ ሆኖ ሲመጣ በሽታው ቀለል ይለዋል፡፡

በእርግጥ ይኼኛውን ነገር ኢሕአዴግን ሆኖ ለሚያስብ ሰው አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል፡፡ ዋናው ችግር የሕወሓትን ግርማ ሞገስ የሚያኮሰምን ነው የሚለው አስተሳሰብ ነው፡፡ በእርግጥ የድርጅቱ አስኳል የሆነው ሕወሓት ለግንባሩ መመሥረት ሚናው ቀላል አይደለም፡፡ ግንባሩ በአንድ ወቅት ውጤታማ ሆኖ ደርግን ጥሏል፡፡ አሁን ግን ጊዜው አይደለም፡፡ ይህንን ሕወሓት ሊያምንና ወቅታዊ መሆኑን ሊቀበል ይገባዋል፡፡ ኢሕዴንን ወደ ብአዴንነት (ከኅብረ ብሔራዊነት ወደ ብሔራዊነት) ያሳነሰ ግንባር፣ ሕወሓትንና ሌሎቹን ወንድሞቹን ወደ ኅብረ ብሔራዊነት ማሳደግ ሊከብደው አይገባም፡፡ የግንባሩ መፍረስ ዛሬም ድረስ ነፃ አውጭ ለሆነው ሕወሓትም (ስሙ የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጭ የሚል መሆኑን ልብ ይሏል) ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ በአንድ በኩል ሌሎቹ የግንባሩ አባላት ለስማቸው መጠሪያ እንኳ ዴሞክራሲ የሚል ቃል ሲያስገቡ፣ ሕወሓት የለውም፡፡ በሌላ ወገን ደግሞ ዛሬም እንደ 1977 ዓ.ም. ይህ ድርጅት ነፃ አውጭ ነኝ እያለ በአማፂ ቡድን ስያሜ ይጠራል፡፡ የቀድሞ ወዳጁ ሻዕቢያ እንኳ ለአፉ ያህል ዴሞክራሲያዊ የምትል ቃል ሰንቅሮ (ሕግዴፍ-ሕዝባዊ ግንባር ለዴሞክራሲና ለፍትሕ) ስሙን ሲቀይር ሕወሓት ዛሬም በቆላ ስሙ ላይ የሙጥኝ ብሎ ቀርቷል፡፡

ድርጅቱ ስም የመቀያየር ችግር የለበትም፡፡ በረሃ ሲገባ ማገብት (ማኅበረ ገስግስቲ ብሔረ ትግራይ) ነበር፡፡ ብዙም ሳይቆይ ተሕሓት (ተጋዳሊ ሕዝቢ ሓርነት ትግራይ) ሲል ራሱን ሰየመ፡፡ በኋላም ሕወሓት (ሕዝበ ወያኔ ሓርነት ትግራይ) ሆኖ አዲስ አበባ ገብቷል፡፡ በየወቅቱ ስሙን የቀያየረበት ምክንያት አሳማኝ እንደሆነ አመራሮቹም ሆኑ አባላቱ ይናገራሉ፡፡ ስለዚህ አሁንም ቢሆን ይህ ድርጅት ስሙን አድሶ ለመምጣት ብዙ ሺሕ ምክንያቶች አሉለት፡፡ የአሁኑ ስም ቅያሬ በእርሱ ፊታውራሪነት የተመሠረተውን ግንባር ንዶ ለዘመኑ የሚመጥን መሆን ይገባዋል፡፡ ይህንን ማድረጉ ጥቅሙ ለራሱም ጭምር መሆኑን የነፃ አውጭው ድርጅት አመራሮች ሊያውቁት ይገባል፡፡ ሉዓላዊ ሥልጣን ባላቸው ክልሎች ላይ ጣልቃ ይገባል፣ ቁልፍ የሥልጣን ቦታዎችን ማጣት አይሻም፣ ከሚለው ወቀሳ ለመዳን፣ ‹‹ይህንን ግንባር ማፍረስ›› የሚለውን ምክረ ሐሳብ ሊቀበለው ይገባል፡፡ የወቀሳው ውሸትነትና ኢ-ምክንያታዊነት የሚረጋገጠውም ይህንን ግንባር ለማፍረስ ሕወሓት ቁርጠኛ ሲሆን ነው፡፡ እንደ ደቡብ አፍሪካ ያሉ ብዙ ባህልና ቋንቋ ያለባቸው አገሮች፣ እንደ ህንድ በስብጥረ ጎሣ የተሞሉ አገሮች የሚመሩት በአንድ ፖርቲ (ANC & BJP) ነው፡፡ እናም ግንባሩ ራሱን ለማደስ የእነዚህን አገሮች ልምድ ማየት አለበት፡፡ ከዚያ መቐለ ላይ ያለው ኢሕአዴግ ሐዋሳ ላይ ካለው ኢሕአዴግ የማይለይ፣ አንድ የሲዳማና አንድ የሽሬ ሰው እኩል የሚያጣጥሙት ይሆናል፡፡

የግንባሩ ሌላኛው ግዙፍ ችግር አግላይ መሆኑ ነው፡፡ ኢሕአዴግ አምስት ክልሎችንና ሁለት የከተማ መስተዳድሮችን አግልሏል፡፡ ኢሕአዴግ ማለት የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ማለት ነው፡፡ ግን ግንባሩ አራት ክልሎችን ብቻ የሚያስተዳድሩ ድርጅቶች ያዋቀሩት ነው፡፡ ‹‹ሌሎቹ ክልሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች አይደሉም ለማለት ነው?›› ወይስ ‹‹እነዚህኞቹ ዴሞክራሲም አብዮትም አያስፈልጋቸውም›› ለማለት ነው አምስቱን ክልሎች ትቶ ሁለት ከተማ መስተዳድሮችን ረስቶ ግንባር ነኝ ማለት?! በምርጫ ሰሞን እየገጠመ ያለው ጉዳይም በቀላሉ እየታለፈ ነው፡፡ አዲስ አበባና ድሬዳዋ ላይ ለመወዳደር ኢሕአዴግ ማሠለፍ ያለበት ግንባሩን ከመሠረቱት አባል ድርጅቶች ብቻ ነው መሆን ያለበት፡፡ ኢሕአዴግ ራሱ ፓርቲ ሆኖ መምጣት አይችልም፡፡ እርሱ ግን እንዲያ እያደረገ ነው፡፡ ጎንደር ላይ ብአዴንን ሆኖ ይሠለፍና አዲስ አበባ ላይ ኢሕአዴግ ሆኖ ነፍስ ይዘራል፡፡ ወለጋ ላይ ኦሕዴድ ሆኖ ይቀርብና ድሬዳዋ ሲደርስ መለያውን አውልቆ በኢሕአዴግነቱ ይሠለፋል፡፡ ስለዚህ በሁለቱ ከተሞች ላይ ኢሕአዴግ የሚባል ግንባርም ፓርቲም እስከሌለ ድረስ ይህንን ጥምረት ወደ ውሕደት ማምጣት መከራከሪያ ሊቀርብበት የማይገባ እውነት ነው፡፡ እናም ወቅታዊው ተሃድሶ ይህንንም ማጤን ይገባዋል!!! የግንባሩ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መግለጫ ግን ያለበትን ችግር ከሙስና ጋር ብቻ አያይዞ ማቅረቡ፣ ለዚህ ጉዳይ ትኩረት እንዳልተሰጠው የሚያመለክት ነው፡፡

የርዕዮተ ዓለም ጉዳይ

የኢሕአዴግ የፖለቲካ ማጠንጠኛ ከአልባኒያ ሶሻሊዝም እስከ ነጭ ካፒታሊዝም ይደርሳል፡፡ ብዙ የርዕዮተ ዓለም ጃኬቶችን አውልቆ ለብሷል፡፡ አሁን ግን ምን ዓይነት መለያ እንደለበሰ ግልጽ አይደለም፡፡ አብዮታዊ ዴሞክራሲ፣ ልማታዊ ዴሞክራሲ የተባሉ ጃኬቶችን ደራርቦ እንደለበሰ ግን እሙን ነው፡፡ ቢያንስ የግንባሩ ስም ላይ ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› የሚሉ ቃላት ስላሉ ድርጅቱ ይህንን ርዕዮት ያቀነቅናል ማለት ነው፡፡ በሌላ ወገን ደግሞ ልማታዊ ዴሞክራሲ የግንባሩ ኅልዮት መሆኑን ከ1993 ዓ.ም. ወዲህ የታተሙ የድርጅቱ ሰነዶች ያስነብባሉ፡፡ እነዚህ እርስ በራሳቸው የሚጣረሱ ጽንሰ ሐሳቦች ናቸው፡፡ ልማታዊ ዴሞክራሲ ፖለቲካዊ አስተምህሮ በአጭሩ ልማትንና ዴሞክራሲን አብሮ ማስኬድ፣ ሁለቱንም ወደ ውጤት ማምጣት የሚል ትርጉም እንዳለው ግንባሩ ደጋግሞ ጽፏል፣ ተናግሯል፡፡ ስለአብዮታዊ ዴሞክራሲ ግን ከጥቂት ነባር አመራሮች በስተቀር በግልጽና በዝርዝር የሚያብራራ ሰው አልታየም፡፡ ከጅምረ ነገሩ ይኼ አብዮታዊ ዴሞክራሲ የሚባለው ርዕዮተ ዓለም ኢሕአዴግ ቆሜለታለሁ ከሚለው መርህ ጋር ይጋጫል፡፡

አብዮታዊ ዴሞክራሲ የማርክሳዊ ኅልዮት ጽንሰ ሐሳብ ነው፡፡ በ1978 ዓ.ም. በአማርኛ ተተርጉሞ የታተመው የማርክሲዝም ሌኒንዝም መዝገበ ቃል ይህንን የፖለቲካ ፍልስፍና እንዲህ ሲል ይገልጸዋል፡፡ ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ ከፊል ካፒታሊስትና በአብዛኛው በቅድመ ካፒታሊስት የዕድገት ደረጃ ላይ በሚገኙ አገሮች ሥልጣን ለመጨበጥ ፀረ-ፊውዳል፣ ፀረ-ኤምፔሪያሊስት፣ ፀረ-ካፒታሊስት የሆነውን ትግል በማርክሳዊ ሌኒናዊ ድርጅት ግንባር ቀደም መሪነት የሚያራምድ ኃይል ነው፡፡›› በዚህ ድሐፍና በግልጽ እንደተቀመጠው ካፒታሊዝምም ሆነ የዚህ ፍልስፍና ወንድም ነፃ ገበያ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ጠላቶች ናቸው፡፡ ኢሕአዴግ በአንፃሩ የነፃ ገበያ ፍልስፍናም ሆነ፣ ነጭ ካፒታሊዝም የምሞትላቸው መርሆዎች ናቸው ብሏል፡፡ ይህ እርስ በርሱ የሚጣረስ ነው፡፡ ጠላት ለሆኑት ፍልስፍናዎቹ እሞታለሁ ማለት የሚቃረን ነው፡፡

በነገራችን ላይ ይህ ፍልስፍና በ19ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በምሥራቅ አውሮፓ፣ በጀርመን (በከፊል) እና በመሰል ሶሻሊስታዊ አገሮች ይተገበር የነበረ አስተሳሰብ ነበር፡፡ ከሶሻሊዝም መንኮታኮት በኋላም ይህ ኅልዮት አብቅቶለታል፡፡ አላበቃለትም ቢባል እንኳ በካፒታሊዝምና በነፃ ገበያ አራማጅ አገሮች ይህ ፖለቲካል ኢኮኖሚ በፍፁም ተቀባይነት የለውም፡፡ በአንድም ካፒታሊስታዊ አገር ውስጥ ይህ ፍልስፍና ገቢራዊ ሆኖ አይገኝም፡፡ ምክንያቱም ፍልስፍናው የወገነው ነፃ ገበያን ከመሳሰሉ የዴሞክራሲ ጽንሰ ሐሳቦች በተቃራኒ ነው፡፡ ይህንን መርህ እከተላለሁ የሚለው የኢትዮጵያ ገዥ ግንባር ግን በቢላዋው ሁለቱም ወገን (በደንደሱና በስለቱ) እየበላ ነው፡፡ ስለዚህ ይህንን ርዕዮተ ዓለማዊ መደበላለቅ ካላጠራ፣ አማራጭ የላችሁም ከሚላቸው ተቃዋሚዎቹ የባሰ ብዥታ ውስጥ ሆኖ ይቀጥላል፡፡ የአንድ ፖለቲካ ቡድን መመዘኛ የሚከተለው ፍልስፍና እንጂ ያሰባሰባቸው ሰዎች አይደሉም፡፡ ኤኤንሲ 106 ዓመቱ ነው፡፡ ይህንን ፓርቲ ከመሠረቱ ሰዎች አንድም በሕይወት የለም፡፡ ሥርዓቱና ርዕዮተ ዓለሙ ግን አብሮት አለ፡፡ ስለዚህ ኢሕአዴግም የሚከተለውን የፖለቲካ ፍልስፍና ማጥራት ወቅታዊ ግዳጁ ሆኖ ተቃርቧል፡፡

የፖሊሲ ተሃድሶ

የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው መግለጫ በ1993 ዓ.ም. ተሃድሶ ማግሥት የተተገበሩ ፖሊሲዎች ውጤታማ ስለመሆናቸውና በአፈጻጸም በኩል ስለገጠማቸው ችግር  የሚተርክ ነው፡፡ በአጭር ቋንቋ ‹‹ፖሊሲዎቹ ውጤታማ ናቸው›› ተብሏል፡፡ ስለዚህ ኢሕአዴግ የፖሊሲ ተሃድሶ ለማድረግ ቁርጠኛ አይደለም ማለት ነው፡፡ ግን በጣም ብዙ ጉዳዮች ፈጣን ለውጥ ይሻሉ፡፡ ዋነኛው ግን የግብርና ፖሊሲ ነው፡፡ ታዋቂው ደራሲ ግርሃም ሃንኩክ “Ethiopia; The Challenge of Hunger” የሚል መጽሐፍ አለው፡፡ በዚህ መጽሐፉ ላይ እንደሚተርከው፣ ይቺን አገር ድርቅ የተባለ መዓት የሚቀጣት ከ13ኛው ክፍለ ዘመን አንስቶ ነው፡፡ ለዘጠኝ ክፍለ ዘመናት የተጣባንን ድርቅና ረሃብ የኢትዮጵያ ግብርና ዛሬም ሊቋቋመው አልቻለም፡፡ ደርግ የተባለው ቡድን ወደ ሥልጣን የመጣው ንጉሡን፣ ውሻቸውንና ቅምጥል ኑሯቸውን ከወሎ ረሃብተኞች ጋር አነፃፅሮ የሚያሳይ ቪዲዮ ለሕዝብ ቀድሞ በማድረስ ነበር፡፡ ሕዝቡ በጃንሆይ ላይ እንደተቆጣ ካረጋገጠ በኋላ ከዙፋን አውርዶ አሠራቸው፡፡ ሥርወ መንግሥቱም ላይመለስ ተገረሰሰ፡፡

ከዓመታት በኋላ በ1977 ሌላ ረሃብ፣ ሌላ ድርቅ ከደርግ መንግሥት ጋር ተፋጠጠ፡፡ ስሙንም ‘የተፈጥሮ መዛባት’ ሲል ጠራው፡፡ የወሎና የትግራይ ጉዳተኞች ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ግን ኮተቤን እንዳያልፉ ትዕዛዝ የሰጠው ይኼው ጁንታ ነበር፡፡ በዚያው ሰሞን በረሃ ላይ ከነበሩት አማፅያን አንዱ ሕወሓት ነውና አቶ መለስ ዜናዊ ለቢቢሲ እንዲህ አሉ፡፡ ‹‹እየተዋጋሁለት ያለሁት ሕዝብ በምግብ እጦት እየሞተ ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ጠንካራ ሠራተኛ ነው፡፡ ግን በድጋፍ ማጣትና ሳይንሳዊ ግብርናን ባለመተግበሩ ሕዝቡ እየሞተ ነው፡፡ ስህተቱ ግን ከእነሱ አይደለም፡፡›› በወቅቱ የሕወሓት ሥራ አስፈጻሚ አባል የነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ የተናገሩት ለረሃቡ ተጠያቂው ሕዝብ ሳይሆን መንግሥት ነው፣ ገበሬ ሳይሆን ፖሊሲ ነው የሚል ይዘት ያለው ነው፡፡ ግን የአቶ መለስ ድርጅት ወደ ሥልጣን መጥቶም አገሪቱ ጠኔ አልተለያትም፡፡ በተደጋጋሚ የተከሰተው ድርቅ ብዙ ሕዝብ ፈትኗል፡፡ በእርግጥ በረሃብ የሞተ ሰው ስለመኖሩ የወጣ ዘገባ የለም፡፡ በዚህም መንግሥት ድርቅን ተቋቁሜያለሁ የሚል መግለጫ በየዓመቱ እንዲያወጣ ሆኗል፡፡ ይህ ሁኔታም ደርግ ጃንሆይን፣ ኢሕአዴግ ደግሞ ደርግን እንደከሰሰበት ሁሉ ተቃዋሚዎቹ በዚህ በኩል ኢሕአዴግን ሲከስሱት አይደመጡም፡፡ 10.2 ሚሊዮን ሕዝብ አፋጣኝ ምግብ ያስፈልገዋል ሲባል እንኳ ተቃዋሚዎቹ፣ ‹‹መንግሥት ድርቁን አልተቋቋመውም›› ብለው ሲናገሩ አልተሰሙም፡፡ ግንባሩ ከነችግሮቹ ድርቁን በጊዜያዊነት መክቶታል፡፡ ድርቅን መቋቋም የተቻለው ግን አገሪቱ ከድሮው የተሻለ የውጭ ግንኙነት መርህ ያላት በመሆኑ (ርዕዮተ ዓለም ላይ ያልተመሠረተ) እና ለጋሽ አካላት እጃቸው ስላላጠረ እንጂ፣ ውጤታማ የሆነ የግብርናና የኢንዱስትሪ ፖሊሲ ስላለን አይደለም፡፡ ይህንን ማመን ለኢሕአዴግ ፈታኝ ቢሆንም ሊያጤነው ግን ይገባል፡፡

አቶ በረከት ስምዖን የሁለት ምርጫዎች ወግ በተሰኘው መጽሐፋቸው፣ የኢትዮጵያ ገበሬ ድህነት ሰበቡ ስንፍናና ለሥራ የሚሰጠው ጊዜ ማነስ መሆኑን እንዲህ ሲሉ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ክረምቱን ብዙ ለፍቶ በበጋ ሠርግና ተዝካር ሲያሳልፍ ጊዜውን የሚያባክነው የኢትዮጵያ አርሶ አደር በዓመት ከመቶ ሃምሳ ቀናት በላይ አይሠራም፡፡ ሃምሳ ሁለት ቅዳሜና እሑዶች በድምሩ መቶ አራት ቀናት ይነጥቁታል፡፡ በክርስትናም ሆነ በእስልምና ሃይማኖቶች ቅዱሳን መጻሕፍቱ ያልከለከሏቸውን ቀናት በዓላት አድርጎ እያከበረ የሚያባክናቸው በርካታ የሥራ ቀናትም አሉት፡፡ በዚህ ላይ ለሠርግና ተዝካር የሚያውለው የሥራ ጊዜ አለ፡፡ በሰሜኑ የአገራችን ክፍል አፍላ የሥራ ወቅት ከሆነው ወርኃ ግንቦት ሁለት ተከታታይ ሳምንታት የጰራቅሊጦስን በዓል ለማክበር ሲባል ሥራ ይፈታበታል፡፡ እነዚህ ሁሉ ተዳምረው በዓመት ሦስት መቶ ቀናት መሥራት የነበረበት አርሶ አደር ቢያንስ ከሁለት መቶ ቀናት በላይ ያርፋል፡፡››

ይህ ጉዳይ እንደ አንድ ምክንያት ሊጠቀስ የሚችል እንጂ መሠረታዊ ሰበብ አይደለም፡፡ ነገርየው በቀጥታ ከፖሊሲ ጋር የሚገናኝ መሆኑን ታውቆ የኢትዮጵያን ገበሬ ከድህነት፣ ከረሃብና ከኋላ ቀርነት ማላቀቅ ወቅታዊ ነው፡፡ በየትም ዓለም በግብርና መር ኢኮኖሚ ያደገ አገር የለም፡፡ ኢሕአዴግ ምሳሌዎቼ ናቸው የሚላቸው እነ ደቡብ ኮሪያ እንኳን ፈጥነው ያደጉት በኢንዱስትሪ መር ፖሊሲ ነው፡፡ በቻይና ከሦስት አሥርታት በፊት 75 በመቶ የሚጠጋ ሕዝብ ገበሬ ነበር፡፡ አሁን ከ50 በመቶ የላቀ ቻይናዊ ኑሮው ከኢንዱስትሪ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በኢንዱስትሪ ላይ የተመሠረተ ምጣኔ ሀብት ለውጭ ንግድም ሆነ ለዘላቂነት፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራም ሆነ ዝናብ ላይ ላልተመሠረተ አስተማማኝ ዕድገት ወሳኝ መሆኑ በተግባር ተረጋግጧል፡፡ ኢሕአዴግ ወደ ሥልጣን ሲመጣ 85 በመቶ የሚሆነው ኢትዮጵያዊ ገበሬ ነበር፡፡ ለዚያውም ኋላቀር በሆነ እርሻ ላይ የተመሠረተ፡፡ ከ26 ዓመታት በኋላ ይኼ አኃዝ ዝቅ ያለው በሁለት በመቶ ብቻ ነው፡፡

ስለዚህ ዛሬም ግብርና ትልቁ ቀጣሪ፣ ትልቁ የውጭ ምንዛሬ ምንጭና ዋነኛው ኋላቀር ሴክተር ነው ማለት ነው፡፡ በአጭር አገላለጽ ዛሬም ለኢንዱስትሪ ሊሆን የሚገባው መሬትና ወደ ከተሜነት ሊያድግ የሚገባው ሕዝብ ብዙ ነው፡፡ እናም የገጠር ዕደ ጥበባትን በማሳደግ፣ ትናንሽ ከተሞችን የመለስተኛ ማቀነባበሪያዎችና የኢንዱስትሪ ማዕከላት በማድረግ፣ ወዘተ. በዚህ በእርሻ ክፍለ ኢኮኖሚ ላይ የሚኖረውን ሕዝብ መቀነስ ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ ደግሞ የመሬት ፖሊሲውን በድጋሜ ማጤን ግድ ይሆናል፡፡ ‹‹መሬት መሸጥ መለወጥ የሚቻለው በኢሕአዴግ መቃብር ላይ ነው›› የሚለውን ደረቅ መከራከሪያ ግንባሩ ሊከልሰው ያስፈልጋል፡፡ ቢያንስ እንደ ወዳጁ ቻይና በከፊል መሬት የሚሸጥበትንና የሚለወጥበትን መንገድ ማመቻቸት፣ ለዚህ የሚሆን ጠንከር ያለ የሕግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ ይህ ፖሊሲ ቢሻሻል ሊኖረው የሚችለው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ብዙ መሆኑ ሊታመንበት ይገባል፡፡ ኢሕአዴግ ለሚቀጥሉት ዓመታት የሚተገበር ተሃድሶ አደርጋለሁ ሲልም፣ ለዚህ አገሪቱን ለተጣባው ድህነት የሚሆን መሠረታዊ ለውጥ በማምጣት ሊሆን ይገባዋል፡፡

የሕገ መንግሥት ማሻሻያ

የ1987 ዓ.ም. ሕገ መንግሥት ወደ 22ኛ ዓመቱ እየተንደረደረ ነው፡፡ ይህ ርዕሰ ሕግ ሲፀድቅ የአገሪቱ ሕዝብ 57 ሚሊዮን ነበር፡፡ ከዚህ ውስጥ ደግሞ በወቅቱ ከ15 ዓመት በላይ የነበረው ሕዝብ 51 በመቶ ያህሉ ነው፡፡ ከዚህ መካከል በሕገ መንግሥቱ ረቂቅ ላይ የተወያየው 16 ሚሊዮን ብቻ መሆኑን መንግሥት በተደጋጋሚ ገልጿል፡፡ ይህ ማለት 41 ሚሊዮን ሕዝብ የአሁኑ ሕገ መንግሥት ሲፀድቅ ተሳታፊ አልነበረም ማለት ነው፡፡ ከ1987 ዓ.ም. ወዲህም የሕዝብ ቁጥሩ ጨምሮ 100 ሚሊዮን መድረሱ እየተገለጸ ነው፡፡ በዚህ አኃዝ መሠረት ሰማኒያ አምስት ሚሊዮን የሚጠጋ ኢትዮጵያዊ ባልተወያየበት፣ ባልወሰነበትና ባልተሳተፈበት ሕገ መንግሥት እየተመራ ነው ማለት ነው፡፡ በዚህ አመክንዮ ብቻ አዲሱ ትውልድ ይህንን ሕገ መንግሥት እንደገና እንዲመክርበትና እንዲያሻሽለው፣ የራሴ ብሎም እንዲቀበለው ማድረግ የኢሕአዴግ ወቅታዊ ኃላፊነት መሆን አለበት፡፡

ከዚህ ከተጠቀሰው ምክንያት ውጪ በራሱ ሕገ መንግሥቱ እንዲሻሻል የሚያስገድዱ ምክንያቶች ብዙ ናቸው ብለው ምሁራንና ፖለቲከኞች ይሞግታሉ፡፡ በተለይ ሙሉ በሙሉ ሕገ መንግሥቱ ከኢሕአዴግ ማኒፌስቶ የተቀዳ መሆኑ ከፖለቲካ ድርጅትም በላይ የሆነ ሰነድ እንዳይሆን አድርጎታል፡፡ ከዚህም ባሻገር ስለተጋነነው የፌዴሬሽን ምክር ቤት መብት፣ ገደብ ስላልተደረገለት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የሥልጣን ዕድሜ፣ እስካሁን ድረስ እያጨቃጨቀ ስላለው ብሔር ተኮር ፌዴራሊዝም፣ የመገንጠልና ራስን በራስ የማስተዳደር መብት፣ የመሬት አጠቃቀም ግዴታዎች፣ ወዘተ. አንኳር የውይይት አጀንዳዎች ሆነው ሕገ መንግሥቱ ላይ ድጋሜ ትኩረት (Reconsideration) ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ ለዚህም ሕዝቡም ሆነ የፖለቲካ ድርጅቶች በግልጽ ውይይትና ክርክር ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ ይህንን ለማድረግ ግን ግንባሩ ቅድሚያ ፈቃደኝነቱን ለአደባባይ አውጥቶ ሊያሳይ ያስፈልጋል፡፡ ይህንን ለማድረግ የሚያስችል ሀብት (Resource)፣ መዋቅርና ተቋማት ደግሞ ከ1987 ዓ.ም. በላቀ ሁናቴ አሉ፡፡ በመሆኑም ቢያንስ 50 በመቶውን ሕዝብ ማወያየት ይቻላል ማለት ነው፡፡

በአጠቃላይ ኢሕአዴግ አንዳንድ ከፍተኛ አመራሮቹን በእስር፣ በጡረታ፣ በዝቅተኛ ሹመት፣ ከኃላፊነት በማንሳት፣ ወዘተ. ገለል አድርጎ ሳያበቃ ፖለቲካዊና ሥር ነቀል ለውጥ (Fundamental POlitical Reformation) አድርጎ ከላይ በተጠቀሱት ሐሳቦችም ላይ ሆነ በሌሎች መርሆዎች ላይ ግብልጥልጥ ያለ መልክ ይዞ ሊመጣ ይገባዋል፡፡

ማነው ተሃድሶ የሚያደርገው?

በአንድ የፖለቲካ ድርጅት ውስጥ ውጫዊና ውስጣዊ ምክንያቶች ተሃድሶ ወይም ለውጥ ይደረጋል፡፡ በአበዳሪዎች፣ በለጋሾች፣ በወዳጅ አገሮች፣ በውጭ ጠላቶች፣ ወዘተ. ግፊት የሚካሄደው ተፅዕኖው ውጫዊ ነው፡፡ በሕዝብ ፍላጎት፣ በፖለቲካ ድርጅቱ ፖሊሲዎች ማርጀት፣ በአመራሮች ድክመትና ግለኝነት፣ በአመራሮች አለመግባባት ወዘተ. ጊዜ የሚካሄደው ተሃድሶ ደግሞ ውስጣዊ ምክንያቶች የሚወልዱት ነው፡፡ ኢሕአዴግ ለተሃድሶ እጁን እንዲሰጥ ያደረገውም ይኼው ሁለተኛው ምክንያት ነው፡፡ በፖለቲካ ተሃድሶ ወቅት አስጊው ነገር ቀውስ ነው፡፡ በተለይ ፖለቲከኞቹ አመለካከታቸውን ወደ ደኅንነት ተቋማቱና ጦር ሠራዊቱ ካወረዱት ሊከፋፍሉትና ለአገርም አደጋ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ፕሮፌሰር አሌክስ ዲ ዎል “Upperhand” የሚለው አንድ ተደማጭ ግለሰብ ወይም ቡድን ሊኖር ግድ ነው፡፡ ልክ እንደ ቻይናው ዴንግ ዓይነት፡፡

የ1993 ዓ.ም. ተሃድሶ ያመጣው ለውጥ ምንም ይሁን ምንም አገሪቱን ወደ ቀውስ አለመውሰዱ ግን በብዙ ሃያሲያን ተወድሷል፡፡ ለዚያ ለውጥ የአቶ መለስ ክንድ ጠንካራ ስለመሆኑ አያከራክርም፡፡ ጥያቄው እንዲህ ያለውን ተሃድሶ ኮሽ ሳይል ማፍረጥረጥ የሚችል አካል አለ ወይ የሚለው ነው፡፡ የአቶ ኃይለ ማርያም መንግሥት እንዲህ ያለውን ዕርምጃ በራሱ ላይ እንዳይወስድ የሚያደርጉት ብዙ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ አንደኛው ለ1993 ዓ.ም. የተሃድሶ ፖሊሲዎች አብዝቶ ታማኝ መሆኑና ይህንንም የመለስ ራዕይ (Legacy) አድርጎ መቀበሉ ነው፡፡ ሁለተኛው ልምድ ማነስ ነው፡፡ አቶ መለስ በተሃድሶ ረገድ ተግባራዊ ልምድ ነበራቸው፡፡ በ1969 ዓ.ም. ሕንፍሽፍሽ ድርጅቱን ሊበትነው ሲል በቦታው ነበሩ፡፡ በ1977 ዓ.ም. ድል ባደረጉበት መድረክ መሪ ተዋናይ ሆነው አጠናቅቀዋል፡፡ ከዚያም ባሻገር በደኅንነት መሥሪያ ቤቱም ሆነ በጦሩ፣ በድርጅቱ አባላትም ሆነ በግንባሩ ውስጥ ስማቸው እየጎላ በመጣ ወቅት በ1993 ዓ.ም. የተካሄደው ተሃድሶ በእሳቸው የበላይነት እንዲያበቃ ግድ ሆነ፡፡

እንዲህ በሚለው አኳኋን አቶ ኃይለ ማርያምም ሆኑ ካቢኔዎቻቸው በአብዛኛው ከ1993 ዓ.ም. ተሃድሶ በኋላ የመጡ ፖለቲከኞች በመሆናቸው ጉዳዩ ሊወሳሰብባቸው ብሎም ሊከብዳቸው ይችላል፡፡ የሀቀኛ ፖለቲካ (Genuine Politics) አቀንቃኝ ለሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም፣ የሴራ ፖለቲካን (Political Intrigue) አብዝቶ የሚፈልገው የተሃድሶ ትወራ ሊከብዳቸው ይችላል፡፡ ሌላኛው አጠራጣሪ ጉዳይ ተሃድሶው የሚያመጣውን በጎም ሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ ሙሉ በሙሉ መቀበል የሚችል የኢሕአዴግ አባል፣ አመራር፣ የመንግሥት ባለሥልጣንና ተቋም የመኖሩ ነገር ነው፡፡ ስለዚህ አቶ ኃይለ ማርያም ልምድ ያላቸውን ጡረተኛ ባለሥልጣናትና አማካሪዎቻቸውን እንዲጠቀሙ የሚገደዱበት ምክንያት ብዙ ሊሆን ይችላል!!

ከአዘጋጁ፡-ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው yayeshime02@gmailማግኘት ይቻላል፡፡

 

 

 

 

 

Standard (Image)

እንወራረድ!... ኢሕአዴግ ከራሱ ጋር ታግሎ ይድናል!

$
0
0

በሰላም ተፈሪ  

‘ኢሕአዴግ አበቃለት፣ በፀና ታሟል፣ የታጋዮች ሳይሆን የሙሰኞች ግንባር ሆኗል፣ ብርሌ ከነቃ አይሆንም ዕቃ ...’ ኧረ ሰሞኑ በኢሕአዴግ ላይ ብዙ ተሟረተበት። ይህንን የወቅቱን ወሬና ትንታኔ ተሸክመው መጥተው በስጦታ ላቀረቡልኝ እነ እንትና ኢሕአዴግ ሕመሙን የሚያውቅ ግን መድኃኒት እጁ ላይ ይዞ መጠኑ ሲያጠና ጊዜ እያባከነ ያለ ታማሚ ነው ብዬ ነገሩን ስሞግታቸው፣ የእጁ ነርቭ የሚያዘው የአንጎሉ ክፍል ተጎድቷል መድኃኒትዋን አይውጣትም ሲል ፅኑው ሞጋቼ አሾፈ። እኔም ደግሞ እንወራረድ ኢሕአዴግ ይድናል አልኩኝ። አሪፉ ተሟጓቼ ቂቂቂ... ብሎ ጨዋታችንን በሳቁ አሞቀው። ነገሩ በቃል ከሚቀር በጽሑፍ ይሁን አልኩኝና የጽሑፌ ርዕስ እንዲሆን መረጥኩት። በዚያውም ለሞጋቼና ለመሰሎቹ እንዲደርስ መጻፍ ይበጃል አልኩና እንወራረድ ኢሕአዴግ ይድናል! ብዬ ይኸው ቀረብኩኝ።  

‘ቁም! ማነህ? ስምህን ተናገር፣ መታወቂያ አለህ?’ የሚሉ ጠንካራ ቃላት በየቦታው ወራት ባስቆጠረው ከጥያቄ ወደ ግርግር በተሻገረው አመፅ ምክንያት የሚሰማ ድምፅ ሆኗል። የረሳነው ድምፅ ነበር። ይህ የማንፈልገው ድምፅ የከተማ ጎዳናዎቻችን ድምፅ እንዲሆን እየተመኘና ልከኛውን ጥያቄ እየጠማዘዘና እያቀጣጠለ ያለው ማን ነው? ይህ ነገር ሆድ ይፍጀው ተብሎ የሚታለፍ ጉዳይ አይደለም። የአገርና የሕዝብ ህልውና ጉዳይ ነው።

ወቅቱ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ነው። እንኳን አደረሰን! በአዲሱ ዓመት ዋዜማ ኢትዮጵያውያን በየቀያቸው በሚያነሱት የአዲስ ዓመት መባቻ አብሳሪ የአንድነት ችቦ ባለ ክፉ ምኞትና የሙስና አጋፋሪ ተገፍትረው ይለያሉ። በኢሕአዴግ የሚመራው መንግሥትም ጉንፋንና አተት እየሆኑ ያስቸገሩት ደቃቅና ግዙፍ መዥገሮችን ጠራርጎ ራሱን ያድናል። እንወራረድ ምኞቴ ከንቱ ምኞት አይደለም፡፡ ኢሕአዴግ በቂ ሕክምና አድርጎ መድኃኒቱን በራሱም በሕዝብ እጅም ተግቶ ይድናል፣ አገሪቱንም ይታደጋል። ኧረ ‘የኢሕአዴግ በሽታ ጉንፋን ብልህ አታቃለው ከጉንፋን በላይ ነው’ አለኝ ሞጋቼ። እሺ ምን ይባል አልኩት? ‘ልብ ድካም ነው’ አለኝ። በሞጋቼ መልስ እኔም፣ እሱም፣ አብረውን የነበሩትም ሁላችንም የምር ሳቅን። ፖለቲካ አዘል ወሬ እንዲህ እየተፎጋገሩ ማውራት የተለመደ ይሁን አይሁን ለአንባቢያን ልተወውና ሁላችንም ግን እስክናነባ ስቀናል። ከሳቅ ከተመለስኩኝ በኋላ እሱንም ቢሆን ቡና፣ ሲጋራ፣ አልኮል ... ስታቆም ይድናል ብዬ ሳልጨርስ ሚጢጢዋ የእኔ ቲፎዞ ‘ኢኮኖሚ ይጎዳል’ ብላ ነገሩን ስታጦዘው የመጀመሪያው ሳቅ ተደገመ። ከሳቅ ስንመለስ እንወራረድ ኢሕአዴግ ይድናል! አልኩኝ። እሺ እናስይዝ ተባለ። ምን? ስንት? ስንል እንዲህ ዓይነት ውርርድ በቀነ ገደብ መወሰን ስለሚከብድ አይሆንም ተባለ። እኔ የሁለት ወር ጣሪያ ይቀመጥለት አልኩኝ። ሞጋቼ ሊያበቃለትም ሊድንም ይህ ጊዜ አይበቃም አለ። እሺ የራስህ የጊዜ ሰሌዳ አስቀምጥ ሲባል ‘ምን ይኼ ሥርዓት ሞተ ስትለው ይድናል፣ ዳነ ስትለው ይሞታል’ ብሎ ዝም አለ። እኔ ግን ቀጠልኩኝ።    

ኢሕአዴግ ፖለቲካን በደመወዝና በምንዳ ብሎም በሙስና ቀመር ሳይሆን፣ ከአገራዊ ፍቅር የሚመነጭ ሕይወትን ስለሕዝብ አሳልፈህ በመስጠት አገር የምታቀናበት መሣሪያ መሆኑን የተገነዘቡ  ኢትዮጵያውያን ታጋዮች በውስጥ ስላሉት አዕማድና ችካል ሆነው ያቆሙታል። እንወራረድ!!! የግንባሩ ዋና ዋና አዕማዶች ሦስት ዓይነት መሆናቸው ለሚወራረዱኝ ግልጽ ላድርግ። ኢሕአዴግ ዓምዶቹ እኔ እንደማስቀምጠው አቀማመጥ የሚደለድላቸው ይሁን አይሁን አላውቅም። እኔ ግን ሞጋቼን ማስረዳት ስላለብኝ የእያንዳንዳቸው ስም፣ ይዘት፣ ጠቀሜታና ድርሻ ዘርዝሬ ለሚዛን አቀርባለሁ። የዓምዶቹን ፅናት፣ ታላቅነትና ህያውነት አስረድቼ ሞጋቼ የሚያቀርበውን ፌዝ ይሁን ቁምነገር በእንወራረድ ጽሑፌ ኢሕአዴግ ይድናል እለዋለሁ።    

አንደኛው የኢሕአዴግ ዓምድ የሚታየው ግን የማይታየው አካል መግዛትና ማንቀሳቀስ የሚችል ብርቱው ኃይል “ሐሳብ” (Idea) ነው። ኢሕአዴግ የኢትዮጵያን ሰላም፣ ፍትሕ፣ ዕድገት፣ ልማት፣ ዴሞክራሲ ... የሚሉ ሐሳቦች ማቆሪያ የመጠሪያ ስም ነው ልንለው እንችላለን። እነዚህ ሐሳቦች ደግሞ በተፈጥሯቸው እየፋፉ ወይም እየቀጨጩ የመሄድ ፀባይ ይኖራቸው ይሆናል። ነገር ግን ዘለዓለማውያን እንጂ ተሰባብረውና ተበታትነው የሚጠፉ ግዑዛን አይደሉም። ስለዚህ ኢሕአዴግን እየሞረዱ ከዝገቱ እንዲነሳ የሚያስችሉት ተፈጥሯዊ የሐሳብ ዓምዶች አሉት ማለት ነው። በመሆኑም  ዘመን ያሻገሩት ግን ደግሞ የደከሙትና የዛጉት ሐሳቦች በዘመናዊ የሐሳብ ሞረድ ይሞርዳቸዋል፣ መልሶ ያንፀባርቃል፣ ይድናል። በህያዋን ዘንድ ከሐሳብ በላይ ብርቱ መሣሪያ የለም። ምክንያቱም እሱ የሁሉም ተፈጣሪዎች መጀመሪያ ነው። ኢሕአዴግም በቀና ሐሳቦች የተፈጠረ በመሆኑ ብርቱ ሆነው የሚታዩትን እያሸነፈ እዚህ ደርሷል ስል ሞጋቼ ነጠቀኝና ‘እውነት ነው ግን? በአዳዲስ ሐሳቦች የተፈጠሩ ብርቱ ጠላቶች ገጥመውታል’ ካለ በኋላ ‘እነሱም አደገኛ ራስን የማበልፀግ ሐሳብ የወለዳቸው የሕዝብ አደራን መርሳት፣ የሕዝብና የአገር ፍቅር መመናመን፣ ፍትሕ በመደለያ መፈጸምና ሌሎችም’ አለኝ። ‘እነዚህም የሐሳብ ልጆች መሆናቸውን አትርሳ’ ብሎ ጨዋታውን ወደኔ ወረወረው።

ጥሩ ያልካቸውም የሐሳብ ልጆች ናቸው። ግን እነዚያ ነገሮች ለኢሕአዴግ ዲቃላ ሆነው የገቡበት ሐሳቦች እንጂ የፈጠሩት ወይም የወለዳቸው አይደሉም ስለው፣ ‘የሁለቱም ሐሳቦች ፍሬ ግን እየታየ ነው’ አለኝ። ሞጋቼ ‘ሳይበዙስ ይቀራሉ ብለህ ነው?’ ብሎ አፌዘ። ‘ደግሞ አትናቀው የእነሱም ሐሳብ ነው አዕምሮና ጊዜ ፈሶበታል’ ብሎ ጨመረ። አስደሳቹ ነገር ሁለቱም በውስጡ መኖራቸውን ኢሕአዴግ ማወቁ አሁንም የሐሳብ ብርታቱ ነው ስለው፣ ‘ማወቅ ብቻ በቂ ነው እንዴ?’ አለኝ። አይደለም ስል ‘በል ተፈጥሮአዊ ሐሳቦቹን በድሪቶ ተሸፍነውበት የመጠቃቀም ሐሳቦች አንፀባራቂ ሆነዋል’ ብሎ ደመደመ። የሞጋቼ የሐሳብ ክብደቱና እውነተኛነቱ ተፈታተነኝ። ግን ዲቃላውን ሐሳብ ለመለየት ሌት ተቀን ሐሳብ እያፈለቀ፣ ሕግ እያረቀቀ፣ በቅጣት እያስተማረ የሚታገል ጤነኛ አካል አለ ብዬ ስጀምር ቀናኝ መሰለኝ፣ እኔና ሞጋቼም ብንሆን እንዲሁ እየተሟገትንም ዲቃላውን ሐሳብ አንደግፍም አይደል? ስለው ‘አዎን’ አለኝ። ስለዚህ ለብርቱ ጨለማ ትንሽ ብርሃን ትቀደዋለች እንደሚባል ሕዝብ የማስደሰት አገር የማቅናት ሐሳብ ያላቸው የኢሕአዴግ ሰዎችም የበለጠ ያንፀባርቃሉ። ስለዚህ ኢሕአዴግ በሐሳብ ይነሳል፣ እያሻሻለ ይገሰግሳል... እንወራረድ! በቀናዎቹ ሐሳቦች ተደግፎ ኢሕአዴግ ይድናል።

ሁለተኛው ዓምዱ የማይታየው ረቂቁን ሐሳብ የሚሸከሙ ታማኝ ታጋዮቹ ናቸው። ‘ኧረ አንተ ሰው ብትሰማኝ ምን አለበት?’ የሚል ዘፈን አቀነቀነብኝ። ቀጥሎም አሁን በዚህ የእንብላ እንብላ ዘመን ኢሕአዴግ ታማኝ ታጋዮች አሉት ብለህ ደፍረህ ትናገራለህ እንዴ? ያለኝ ሰው አውቀዋለሁ። ስሙን አልጠራም እንጂ ድምፁን ሰምቸዋለሁ። አዎ ኢሕአዴግ ታማኝ ባለአደራ ታጋዮች አሉት። እነማን? የምትል በፌዝ ቃና ጣል የተደረገች ድምፅ ሰምቻለሁ። ግን ማን ሞኝ አለ ወዳጁን ለበላተኛ ጥርስ አሳልፎ የሚሰጥ በማለት እኔም ስም አልጠራም አልኩኝ። ይሁን እንጂ እንወራረድ ኢሕአዴግ አደራቸውን ያልበሉ ታጋዮች አሉት ብዬ ቀጠልኩኝ። በቅርብ ያለው ሞጋቼ ‘ስንት ይሆናሉ?’ አለኝ ። የብዛት ሳይሆን የጥራትና የፅናት ኃያልነትን ለሚያምን አሁንም ኢሕአዴግ የሚያድኑት ታጋዮች እንዳሉት ሳብራራ አሪፉ ሞጋቼ፣ ‘ደጋግመህ አስብ’ አለኝ። ወደ ፊት ወደ ኋላ፣ ወደ ግራ ወደ ቀኝ አልኩና በኢሕአዴግ ውስጥ የሕዝብና የአገር ፍቅር የሚያንገላታቸው ታጋዮች እንዳሉት አስረገጥኩኝ። ጠያቂ መሆን እንዴት ቀላል ነው። ገንዘብ ... ያላሸነፋቸው እነማን ናቸው? ብሎ አፋጠጠኝ። ግን ለምንድነው ስለግለሰቦች እንድናወራ የምትገፋፋኝ ስለው ‘መገለጫ ለማግኘት ነው’ አለ። ‘ደግሞም እያጠፉም እያለሙም ያሉት ሰዎች ናቸው። በወረቀት ያሉ ቀለማት አይደሉም’ ብሎ ተቀናጣ። የመጀመሪያውን ዓምድ ሳስረዳህ ኢሕአዴግ ሐሳብ ነው ብያለሁ። ስለሆነም እነዚያ አሉት የምልህ ታጋዮች የድርጅቱን መልካም እሴት የደፈነውን ገለባ በመንሽ እየገለጡ የታፈነውን መልካም ዘር እያወጡ መልሰው ቆፎ ይሞላሉ፣ አገር ይሆናሉ አልኩት። ‘አሁን ያልከው ከሽለላና ከቀረርቶ በምን ይለያል?’ እንዳለኝ ውስጤ ደግሞ እንዴት ያሳዝናል አለኝ። ምኑ ብዬ ሳልጠይቀው? ‘የምትወደውን መከላከል ሲያቅትህ’ ብሎኝ ጠፋ።

እኔም ለሞጋቼ እንዲህ አልኩት። አንኳሮቹ የኢሕአዴግ የሙስና አለቆችና የሌብነት መንገዶቻቸው የምትላቸውን ንገረኝና በእያንዳንዱ ላይ ሐሳብ እንስጥ አልኩት። ‘ይሻላል ብለህ ነው?’ አለና ‘ባልከው አቀራረብ ከሄድኩኝ ለአንተ የሚከብድህ ይመስለኛል’ የሚል ንግግር ጠብ አድርጎ ኢሕአዴግ አበቃለት የምልበት ዋና ምክንያት “የፖለቲካ ሙሰኝነቱ” ነው ብሎ ከባድ ሐሳብ ቁጭ አደረገ። ቀጥሎም ‘እንደ ጆሮ ጠቢ ግን ማድረስ የለም’ አለ። አጋጣሚው ከተጠያቂነትና ከተከላካይነት የሚያስወጣ መንገድ ሆነልኝና እንዴት? ብዬ ጠየቅኩኝ። ‘ኢሕአዴግ መሞት የጀመረው ቅድም ያልከውን ብርቱ የሐሳብ ዓምድ መሸከምም ሆነ መደገፍ የማይችሉ በብቃት፣ በንቃት፣ በዕውቀት፣ በሕዝባዊነት፣ በአገራዊ ፍቅር፣ በያገባኛል ባይነት በነፃነት የማይጠይቁ “ሰምቶ አደሮች” በማብዛቱ ነው’ ብሎ ሐሳቡን አጠናከረው። ‘ይህ የተሳሳተ መንገዱ በደም ሥራቸው የዚህች አገርና የድርጅቱ ፍቅር ያነደዳቸው ታጋዮቹ አራት ኪሎ ካደረሱት በኋላ በልቷል’ አለኝ። ‘ምክንያቱም የድርጅቱ አለቆች ሰሚ እንጂ የተለየ ሐሳብ ያለው ተሟጋችና ተተኪ በቀና ማየት አልፈለጉም። ቆንጆዎቹን ታጋዮች በመብላቱ የድርጅቱ እውነተኛ ማንነት ወደ ሕዝብ ሳይዘልቅ ቀርቷል። ይኼ ተግባሩ የራሱ ጉዳይ እልህ እችል ነበር ነገር ግን ከእነዚያ የምር የሕዝብና የአገር ፍቅር ያነደዳቸው በርካታ ታጋዮች መልካም ልምድና ተሞክሮ ማግኘት ይችል የነበረው ዜጋ በተገላቢጦሽ እየተማረ ነው።’ በተገላቢጠሽ? ስትል አልኩት። አየህ አሁን መንግሥት በሠፈራችን፣ በቢሯችን በዩኒቨርሲቲያችን የምናውቀው ሰነፍ ሰው ይሾማል፣ ይሸልማል። ማንም ሰው ደግሞ ተሿሚ ተሸላሚ መሆንን ይፈልጋል። ስለዚህ ሰነፍ መሆን በኢሕአዴግ ለሹመትና ለሽልማት ሲያበቃ ጎበዝና ጠያቂ መሆን ደግሞ ለውርደት ይዳርጋል’ ብሎ ‘ትውልዱ ተፈጥሮ በሰጠችው አዕምሮ ይደመድማል። ምክንያቱም ከአለቃው ጋር ተመሳስሎ አገር ቢፈርስም ዝም ብሎ የአለቃ ቃል እያከበረ ራሱን፣ ቤተሰቡንና ቻይናን እያበለፀገ የሚኖር ሰው ምንም እንደማይሆን ይመለከታሉ። ይህ አቅጣጫ ኢሕአዴግ አገር እያለማ የአገርም የራሱንም እሴት የጎዳበት ታሪኩ ነው።

‘ይኸው እንዲህ ያሉ ሰዎች የአገሩን ገንዘብ ዝቀውታል፣ ፍትሕ አጉድለዋል ኢሕአዴግንም ከሕዝብ ጋር አጣልተውታል። በነገራችን ላይ እነዚህ የኢሕአዴግ ሰዎች ከሁሉም የኢትዮጵያ አከባቢዎች የተገኙ ናቸው። በመሆኑም በሽታ ዘርፈ ብዙ ነው’ ብሎ ዘነጠብኝ። ያበቃል ስል ‘አየህ?’ ብሎ ቀጠለ። ቻይናውያን በቢሊዮን ብር ሊያተርፉ በመቶ ሺዎች ጉቦ ተቀብለው ያለ ደረጃው መንገድ የሚመርቁ፣ የትርፍ ድርድራቸውን እንኳን ከፍ አድርገው የማይወስዱ ሰነፎች የበረከቱባት አገር ሆነች። የሰነፎች ቤት ደግሞ ይፈርሳል ብሎ’ ተስፋ ሊያስቆርጠኝ ሞከረ። ሞጋቼ እመነኝ ታማኝ ታጋዮቹ ያልካቸውን እውነቶች ተቀብለው ለአገርና ለሕዝብ ሲባል የዓሳ ግማቱ በጭንቅላቱ ብለው ያለ ምሕረት በአናት አተኩረው ያጭዳሉ፣ አትሞኝ’ አለኝ። ምን ነው በጌትነት አናት ላይ ያሉ አለቆች ወዛቸውና ልብሳቸው ያስፈራል ብለህ ነው። እመነኝ እነሱ ከአገር በላይ አይደሉም። ከዚያም አልፎ ተያይዞ ለምለሙንና ደረቁን አብሮ ከመጥፋት አደጋውን የፈጠረው ሙሰኛ ማጥፋት ይመርጣሉ። ሕዝቡ ደግሞ ትእምርተ ሙስና የሆኑትን ሲወገዱ ካየ ኢሕአዴግን እንኳን ወደማንነትህ ደህና ተመለስክ ብሎ ይቀበለዋል። ስለዚህ በሁለተኛው ዓምዱም ኢሕአዴግ ይድናል። እንወራረድ! 

ሦስተኛው ዓምድ የልማት፣ የታቀደ ዕድገት፣ የተጻፈ ሕግ፣ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ልምምድና ሌሎች ተስፋዎች የተመለከተ ሕዝብ ነው። ሕዝብ ደግሞ ብርቱ አለንጋ ነው ብዬ ሳልጨርስ ‘ሕዝብማ ኢሕአዴግን እየገረፈ ነው’ አለኝ ሞጋቼ። የሕዝብ ጅራፍ ጤነኛና ለማስተካከል የሚወጣ ነው አልኩኝ። እውነት ነው ለዝርፊያ ታክቲክ ራሱን አብቅቶ ሕዝቡን ያቆሰለ የኢሕአዴግን አካል ቆርጦ ለመጣል የሕዝቡ የጊዜ ጣሪያ ደርሷል። ቢሆንም ሕዝቡ ኢሕአዴግ በሚመራው መንግሥት መሪነት ሊተገብረው ተመኘ እንጂ፣ አገሩን አፍርሶ ቀየውን አውድሞ ሥርዓት አልባ ለመሆን ጅራፉን እንዳላነሳ እርግጠኛ ለመሆን በቅርብ ያለ ሰው መጠየቅ በቂ ነው። ማንም ኢትዮጵያዊ በአገሩ ያየውን ሁለንተናዊ ተስፋ እንዲጨልምበት አይፈልግም። ነገር ግን በታየው ተስፋ ተሸጉጠው ይኸውልህ የእኛ ፍሬ ነው እያሉ መጪውን ዘመን አንቀው የያዙት ታማሚ የኢሕአዴግ አካላት ሸልቶ ለመጣል ሁሉም ኢትዮጵያዊ መቀሱን ይዞ ከጤነኛው የኢሕአዴግ አካል የቆመበት ጊዜ ነው። ምክንያቱም ሕዝብ ... እነማን ነበሩ? ትዝ አለኝ እነ ባለሁለት ዜግነት... እንደነሱ ሌላ አገርና ዜግነት የለውም። ስለዚህ ሕዝብ መንግሥት ሆኖ እየመራ ላለው ኢሕአዴግ ከበሽታው እንዲድን ደማካሴና ጤና አዳም በመሆን ያገለግለዋል። በመሆኑም ኢሕአዴግ በሕዝብ ድጋፍ ይጠራል፣ የበለጠ የእውነተኛ ዴሞክራሲ ማዕከል ይሆናል። እንወራረድ ኢሕአዴግ ከራሱ መዥገሮች ነፃ ይወጣል። የነፃነት ሐዋርያት አፍርቶ ከገባበት ማዕበል በሕዝብ ድጋፍ ይድናል። እንወራረድ! ሕዝቡ ኢሕአዴግን ያድናል፤፣በአዲስ ውበት ቀርፆ ያወጣዋል።

የኢሕአዴግ መዳን አለመዳን በኢትዮጵያ ህልውና ወሳኝ ድርሻ ስላለው የኢሕአዴግን መዳን ተመኘሁ። ምኞቴ እውን እንደሚሆን ለማስረገጥ ከኢሕአዴግ የተፈጥሮ ባህርያት ዋና ዋናዎቹን ለማሳየት ሞክሬያለሁ። አይሆንም የሚል ካለ አሁንም ኢሕአዴግ በሦስቱም ዓምዶቹ ድጋፍ ይድናል፡፡ እንወራረድ!

እርግጥ ነው መንግሥታዊ ሥርዓት እየመራ ያለ ፓርቲ ተቃውሞ ሲበዛበት የማኅበረሰቡ እውነተኛ ወቅታዊ አጀንዳ በበቂ ሁኔታ ማንፀባረቅ ያለመቻሉን ያሳያል። ይህ ማለት ግን ዘላቂ ጠቀሜታ ያላቸው ራዕዮችና ዕቅዶች የሉትም ማለት አይደለም። ነገር ግን በሥርዓቱ የፖለቲካ ልሂቃን የፍልስፍና ቀመር ዋጋ ያልተሰጣቸው ሕዝቡን ግን ጥይት ሆነው ባይገድሉትም፣ መርፌ ሆነው ህሊናውን የሚያሰቃዩት የፍትሕ፣ የዕለታዊ ኑሮ፣ ሌሎች ማኅበራዊና ፖለቲካዊ እርካታ ያሳጡት ነገሮች አደባባይ ሊያስወጡት ይችላሉ። አደባባይ መውጣት ብቻ ሳይሆን ከእነዚህ ችግሮች እፎይታ ለማግኘት የተሳሳተ መንገድ ሊመኝ ይችላል። ታድያ በዚህ ጊዜ የመንግሥት ፖለቲካዊ ብቃቱ ይመዘናል። በመሆኑም አሪፍ ፖለቲከኛ ራሱን ከሕዝብ ፍላጎት ጋር አጣጥሞ ይቀርባል። ኢሕአዴግም በጥቂት ታጋዮቹ ብርታት ከሕዝቡ ጋር ሳይሆን ከራሱ ጋር ትግል አድርጎ ራሱን ያድናል። ለአገሪቱ ወቅታዊ ጥያቄ ፖለቲካዊ መልስ ይዞ ይመጣል። ታድያ መልሱ ያለው እየተበራከቱ ካሉ ሞሎች፣ የተንፈላሰሱ ሆቴሎች፣ ሱፐር ማርኬቶች ወይም ከፖለቲካዊ ብልጣ ብልጥነት አይደለም። መልሱ ያለው ከትግሉ ሰማዕታት መቃብር ነው። ‘ከመቃብር መልስ የለም’ አለ የሞጋቼ ድምፅ።

የሰማዕታቱ መቃብር ሁለት ዓይነት ነው። አንደኛው ሁሉም የአዳም ፍጥረት የሚቀበርበት ሰውና መሬት የሚዛመዱበት ግዑዙ መቃብር ነው። ሁለተኛው መቃብር የህሊና መቃብር ነው። በዚህኛው መቃብርም የትግሉ ሰማዕታት በሁለት መንገድ ይቀበራሉ። ቀዳሚው መቃብር በቀሪው ህያው የትግል ጓድ ህሊና ውስጥ በጥልቀትና በውህደት መቀበር ሲሆን ይህ ዓይነቱ ቀብር በሌላው ታማኝ ጓድ ህሊና፣ ሥጋና ደም ውስጥ ህያው ሆኖ መቀጠል ማለት ነው። እንዲህ ሲሆን ሁሌም ለአዲስ ትግል አዲስ ጉልበትና ስንቅ እየሆኑ በአዲስ ታሪክና ሕዝባዊ ፍቅር እየደመቁ መኖር ይሆናል። ሁለተኛው መቃብር በቀሪው ህያው የትግል ጓድ ህሊና ውስጥ መረሳት ነው። ይህ የከፋ መቃብር ነው። ሁሉም ዓይነት መቃብሮች በገሃዱ ዓለም እውን ሆኗል። ይሁን እንጂ ሰማዕታቱን ከህሊናቸው ጓዳ፣ ከሥጋና ደማቸው በማዋሀድ እያኖሩ ያሉ ታጋዮች እውነተኛው መልስ ከሰማዕታት መቃብር ይዘው ይመጣሉ። ስለዚህ ኢሕአዴግ ይድናል። ሞጋቼ ‘እንዲህ ሊያደርጉ የሚችሉት ሰዎች ቁጥራቸው ጥቂት ነው’ አለኝ። እውነት ነው። ግን እነዚያ ብዙዎችስ ምንና ምን ናቸው? አልኩት። እነሱ ... አስመሳዮች፣ ዘራፊዎች፣ ለአለቃ ተላላኪዎች፣ ለምስኪን ደግሞ ነገሥታት፣ ሙሰኞች...’ አለኝ። አሁንም ስሙን አልጠራውም። ለምን ጠቅለል ባለ ቅፅል ሌቦች አትልም? አልኩት። ዝም አለ። በል ስማ እንኳንስ በባህሪው ደንጋጣና ስግብግብ ከሆነው ሌባ ጋር ከታንኮች፣ በርቀት አልመው ሕይወት ከሚቀጥፉ ዘመናዊ ብረቶችና በሺዎች የሚቆጠሩ የሠለጠኑ ገዳዮች ጋር ጥቂት ታጋዮች ገጥመው ሲፋለሙ የሐሳባቸውን ብርታትና ራዕይ የተመለከቱ እውነተኛ ህሊና ያላቸው ኢትዮጵያውያን ደርሰውላቸው፣ ይኸውና እየተቀባበሉ የምናየው ሁሉ ሆኗል። እመነኝ ይህ ስሜት ከውስጣቸው ያልጠፋባቸው ታጋዮች ኢሕአዴግን እየበሉት ከከረሙና አሁን ሊውጡት ከተዘጋጁ ሆዳሞች አፍና ጥርስ በሕዝብ አጀብ ያድኑታል። እንወራረድ! ኢሕአዴግ ይድናል።

መልካም አዲስ ዓመት!

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው tefyem05@yahoo.comማግኘት ይቻላል፡፡ 

Standard (Image)

ይድረስ “ለሚመለከታችሁ” የፍትሕ አካላት!

$
0
0

በእስማኤል አደም

ዕለተ ማክሰኞ ነሐሴ 3 ቀን 2008 ዓ.ም. በወጣው ዕለታዊው የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ የቀድሞውን የፍትሕ ሚኒስቴርን በማፍረስ በአዋጅ ቁጥር 943/2008 የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን፣ የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን፣ እንዲሁም የንግድ ውድድርና ሸማቾች ጥበቃ ባለሥልጣንን የመክሰስ ሥልጣን አንስቶና የሁሉንም ከሳሽነት በሥሩ አካቶ የተቋቋመው የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ መሥሪያ ቤት አዳዲስ ዓቃቢያንን ለመቅጠር እንደሚፈልግ ገልጾ ማስታወቂያ አስነግሮ ነበር፡፡

በዚህ ከረዳት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ እስከ ዓቃቤ ሕግ ደረጃ ሦስት ድረስ መመዝገብና መወዳደር እንደሚቻል በተነገረበት ማስታወቂያ ላይ የአካል ጉዳተኞች፣ የሴቶችና የ“ብሔር ብሔረሰቦች” ተዋፅኦና ኮታ ከግምት እንደሚገባ ተነግሮም ስለነበር፣ በማግሥቱ በርካታ ሰዎች ከክልል ሳይቀር መጥተው ካዛንችስ አካባቢ ባለው ዋና መሥሪያ ቤት በር ላይ የተሠለፉት በጠዋት ነበር፡፡

ተቋሙ ግን ጋዜጣው ላይ በተለይ ለዓቃቤ ሕግ ደረጃ ሦስት ካስቀመጠው የዜሮ ዓመት የሥራ ልምድ በተጨማሪ ማስታወቂያው ላይ ያልተጠቀሰውን ከ“ፍትሕ አካላት ባለሙያዎች ሥልጠና ማዕከላት” ሥልጠና የወሰዱበትን የትምህርት ማስረጃ ይዘው እንዲመጡ በመጠየቅ ነበር፣ የደረጃ ሦስት “ተስፈኛ” የሆኑ የ2008 ዓ.ም. ተመራቂዎችን ሳይመዘግብ የመለሰው፡፡

እንደ አሠራር ከዩኒቨርሲቲ የአምስት ዓመታት ቆያታ በኋላ ወደ የፍትሕ አካላት ማሠልጠኛ ማዕከላት በፈተናና ማጣሪያ የሚገቡ የሕግ ተማሪዎች ከማዕከላቱ የወራት ሥልጠናቸውን ጨርሰው ሲወጡ፣ በዳኝነትና ዓቃቤ ሕግነት የሚሾሙና የሚመደቡበት የግዴታ አገልግሎትም የሚሰጡበት ሥርዓት እንዳለ ሕጉ አካባቢ ቅርበት ያለን ሰዎች የምናውቀው እውነታ ነው፡፡

ታዲያ በምን መሥፈርት፣ ሥርዓትና አሠራር ነው የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ እነዚህን ሰዎች ለማወዳደር ማስታወቂያ ሊያስነግር የቻለው? ሥልጠናውን ከወሰዱ በኋላ አገልግሎቱን ለመስጠት ፈቃደኛ የማይሆኑ ሰዎች አሉ ማለት ነው? ይህስ አግባብ ነው? ካልሆነስ ተቋሙ ለምን እንዲህ ዓይነቱን አሠራር ፈለገው? … የሚሉ ጥያቄዎች የብዙዎች ሆነዋልና ተቋሙ መልስ ቢሰጥበት የፍትሕ ማዕከላቱም ይህንን ቢያውቁት መልካም ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡

የ “አዲስ አበባውያን” ነገር!

የኢትዮጵያችን ፌዴራሊዝም በዘጠኙ የፌዴራል መንግሥቱ አካላት ላይ ብቻ የተመሠረተ አይደለምና ሁለት የከተማ መስተዳድሮችን ያውቃል፡፡ የድሬዳዋና የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድሮችን፡፡ ድሬ በመስተዳደር ደረጃ ያለች ብትሆንም ከአዲስ አበባ በተነፃፃሪ የአንድ ክልልን (ኦሮሚያን) ባህልና ማንነት በመጠኑም ቢሆን የምታንፀባርቅ ከተማ ስለሆነች፣ ነዋሪዎቿ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥትን መታወቂያ ማግኘት አይከብዳቸውም፡፡ ለድሬዳዋ የሕግ ተማሪዎችም ይኸው ጉዳይ አስቸጋሪ ላይሆን ይችላል፡፡

የኦሮሚኛን ቋንቋ እስከቻሉ ድረስም በኦሮሚያ ክልል የፍትሕ አካላት ማሠልጠኛ ተቋማት በኩል ተወዳድሮ ገብቶ መሠልጠኑም ሆነ ከሥልጠናው በኋላ በተመደቡበት አካባቢ መሥራቱ ለድሬዎች እንግዳና ያልተለመደ አዲስ ነገር አይደለም፡፡

ለእኛ ለአዲስ አበባውያኑስ?

ከወራት በፊት በሸገር ሬዲዮ ላይ ይፋ የተደረገ አንድ የጥናት ውጤት በመዲናችን አዲስ አበባ ብቻ ከሃያ ሺሕ የሚልቁ ሥራ አጥ፣ ግን ደግሞ ሥራ ፈላጊ ወጣቶች እንዳሉ ተገልጾ ነበር፡፡ ዩኒቨርሲቲ እያለሁ ከጓደኞቼ በተለይም ከሕግ ተማሪ ጓደኞቼ ጋር አብዝተን ከምንከራከርባቸው ጉዳዮች አንዱ ፌዴራሊዝማችን የ“አዲስ አበባውያን”ን ማንነትና ፍላጎት ፍፁም የዘነጋ የመሆን አለመሆኑ ነገር አንዱ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡

እንደ እኔው ሁሉ በርካታ አዲስ አበቤዎች የተለያዩ ብሔሮች ድቅል ነን፡፡ ይህ ባይሆንና ከተመሳሳይ ብሔር ብንወለድ እንኳን ከብሔር ማንነታችን ይልቅ የሸገር ልጅነታችን፣ አለፍ ሲልም ኢትዮጵያዊ ዜግነታችንን ነው የምናጎላውም የሚጎላብንም፡፡ አዲስ አበቤዎች የእናታችን ወይም የአባታችን ክልል ሄደን የምናገኘው “የብሔር” መታወቂያ የለንም፡፡ የእናት ወይም የአባታችን ክልል ሄደን ልናገኝ የምንችለው የ“ፍትሕ አካላት” የሚሰጡት ሥልጠናም የለም፡፡ የፌዴራል ሥርዓታችን የሚያውቀን “ለየብቻ” ነውና ለእኛ ለጅምላዎቹ ቦታ የለውም ወይም ሆን ተብሎ ችላ ተብለናል፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ በዘረዘረው መሥፈርት መሠረትም ሆነ አልፎ አልፎ ብቻ ተማሪዎችን የሚቀበለው “የፌዴራል” የሚባለው የፍትሕ አካላት ማሠልጠኛ ማዕከልም ይህንኑ “የብሔር” መሥፈርት የሚጠቀም ተቋም ስለሆነ፣ ለእንደዚህ ዓይነቶቹ የሥራ ማስታወቂያ ውድድሮችና ዕድሎች ተገቢ (Eligible) የሆኑ አመልካቾች የሚመጡት ከክልል የሕግ ተማሪዎች ብቻ ይሆናልና ሸገሮች እንደተለመደው (Business as Usual እንዲሉ!) የበይ ተመልካች ሆንን ማለት ነው፡፡ ብሶት ነውና ይለይለት አይደል?… ሌላ ከዚህም ጠንከር ያለ እውነትን እንደ ምሳሌ ልጨምር፡፡ የጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ ማስታወቂያ ሲወጣ ከተለያዩ ክልሎች ለመወዳደር የመጡ ተማሪዎች እንደነበሩ ከላይ ጠቅሻለሁ፡፡ ከአዲስ አበባውያኑ የሕግ ተማሪዎች በተለየ ለእነዚህ የክልል ተማሪዎች ይህ ተቋምም ሆነ ሌሎች በመዲናዋ የሚገኙ የፌዴራል መንግሥቱ ተቋማት “የዕድላቸው መጨረሻ” አይደሉምና ከተሳካ ተሳካ፣ ካልተሳካም ሥራ አያጡም… ሁለት ጉድጓድ ያላት አይጥ አትሞትም እንዲሉ!

ይህን ጽሑፍ እያሰናዳሁ ባለሁበት ወቅት እንኩዋ እነዚህ የክልል በተለይም የኦሮሚያ፣ የአማራና የትግራይ ክልል ወንድምና እህቶቻችን ወደ ክልላቸው ተመልሰው የየክልሉን የፍትሕ አካላት ሥልጠና ማዕከላት ተቀባይነትን አግኝተዋል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያዎቹም ቢሆኑ የሚጠብቁት የነሐሴን መጋመስና የክልሉን የፍትሕ አካላት ማሠልጠኛ ማዕከል ማስታወቂያ ነው፡፡ እዚህ ላይ ሳልጠቅሰው የማላልፈው አንድ እውነት ደግሞ የአዲስ አበባ ተወላጆች ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ “አባል” የሚሆኑበት የኢሕአዴግ አደረጃጀት ደኢሕዴን (ብዙ ብሔረሰቦችን ያቅፋል ተብሎ ስለሚታሰብ!) ቢሆንም፣ ተማሪዎቹ ተመርቀው ሲወጡ በዚህ ክልል እንኩዋ ሥልጠናም ሆነ ሥራ እንዲያገኙ የሚያስችላቸው ምንም ነገር የለም፡፡ ምክንያቱም ሁሉም ክልሎች ቅድሚያ የሚሰጡትና እንዲሰጡም የሚገደዱት ለተወላጃቸው ነውና፡፡

ብሶት ነውና ይለይለት አይደል?… በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ላሉ ቀውሶች የተማረው ወጣት ሥራ አጥ መሆኑ ተደጋግሞ በመንግሥታችን ሲጠቀስ አድምጫለሁ፡፡ የእኛስ የአዲስ አበቤዎቹ በከንቱ መባዘንስ ምነው ተዘነጋ? አደባባይ ካልወጣን አንደመጥም ማለት ነው!? ውይይቱ “ውይይት” ስለማይሆን የሚያመጣው ለውጥ ይኖራል ብዬ ባላምንም፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በነሐሴ አጋማሽ ከከተማዋ ወጣቶች ጋር ሊያደርጉት የነበረው ውይይት ቢራዘምም ባለፈው ሳምንት ተደርጓል፡፡ እነማንን በምን መሥፈርት፣ የትና መቼ ጠርቶ እንደሰበሰበ ባላውቅም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቅርቡ በየክፍለ ከተማው ወጣቶችን ሰብስቤ አወያይቻለሁ ሁከቱንም እንዲያወግዙ አድርጌያለሁ ሲልም ተደምጧል፡፡

ለመሆኑ ይኼን ያህል ሥራ ፈላጊ ያለባትን ከተማ የሚያስተዳድሩ ሰዎች ለአዲስ አበቤዎች ቅድሚያ የሚሰጡበት የሥራ ዘርፍ ይኖር ይሆን? አዲስ አበባ ምንም እንኳን የፌዴራሉ መንግሥት ማዕከል ብትሆንም፣ ለእኛ ለአዲስ አበባውያን እንደ ክልል ናትና ሌሎች ክልሎች ለተወላጆቻቸው የሚሰጡት ዓይነት ቅድሚያ ሊሰጠን ይገባል ብንልስ ጠባብነት ይሆንብን ይሆን እንዴ?

በነገራችሁ ላይ የሕግ ተማሪዎችን ጉዳይ እንደ ምሳሌ አነሳሁ እንጂ ነገርየው ብዙዎችን የሚመለከት ጉዳይ ነው፡፡ አሁን አሁንማ የግል ድርጅቶችም ሆኑ አክሲዮን ማኅበራት የፖለቲካችንን ጤና ማጣት አሳባቂ ሆነዋልና በግልጽ የማያስቀምጡት፣ ግና እንደ መሥፈርት የሚጠቀሙበት “የብሔር ተኮር” ፉክክራዊ ቅጥር ስለመኖሩ ከአዲስ አበባውያን የተሰወረ አይደለም፡፡ በመንግሥታዊ መሥሪያ ቤቶች በንጉሡ ጊዜ ቀርቶ የነበረው የዘመድ አዝማዳ ቅጥር አሁን ስምና መልኩን ቀይሮ በብሔር ብሔረሰብ የፉክክርና የሃይማኖታዊ ዝምድና መግነን በኩል እየመጣ መሆኑን ሰምተናልም፣ አይተን ታዝበናልም፡፡

አዲስ አበባውያን ታዲያ ተስፋችን ምንድነው? አደገኛ ቦዘኔ ተብሎ መሰደብ አይደለምን? በአዲስ አበባችን ያሉና የሸገሩ ጥናት የጠቆማቸውን ሃያ ሺሕ ሥራ ፈላጊዎች ቁጥር ሃያ ምናምን ሺሕ ገፋ ሲልም ሰላሳ ሺሕ ማድረስ አይደለምን… ታድያ ተመርቆ እንኳን ከቤተሰብ እጅና ድጎማ መውጣት ያልቻለ ወጣት ራዕዩን ቢጥልና ሱሱን ቢያጠናክር ለምን ይፈረድበትና ይተቻል? ብሶት ነውና ይለይለት አይደል?… በርካቶች በኢትዮጵያችን የፍትሕ በተለይ የወንጀል ፍትሕ የማግኘቱ ነገር መጓተት ጉዳይ እንደሚያሳስባቸው ግልጽ ነው፡፡ በተለይ ከፍርድ ቤቶቻችን የወንጀል ፍትሕን፣ ከፖሊስ መከላከያና ደኅንነት ተቋማት የሰብዓዊነት ፍትሕን ማግኘት እየከበደ እንደመጣ መንግሥታችንም አምኖበታል፡፡

የሕግ ተማሪዎች ለሥራ ላይ ልምምድና ለትምህርታዊ ጉዳዮች ወደ ፍትሕ ተቋማት ስንሄድ የምንታዘበው ነገር ቢበረክትም፣ ጥቂቱን እዚህ መጥቀስ ይኖርብኛል፡፡ የመጀመሪያው ነገር ፍርድ ቤቶችን የሚመለከት ነው፡፡ ሌሎች ጉዳዮችን ለጊዜው ትተን በአዲስ አበባችንም ሆነ በክልሎች ለፍርድ መጓተት አንዱ ምክንያት፣ የዳኞች እጥረት እንደሆነና አንድ ዳኛ የበርካታ ሰዎችን ጉዳይ የሚያይ መሆኑ ነው፡፡ በአንፃሩ ሥራ አጥተው ሥራ ፍለጋ የሚንከራተቱና ይህንን ክፍተት መሙላት የሚችሉ ብሎም ራሳቸው ተጠቅመው አገራቸውንና ሕዝባቸውን መጥቀም የሚችሉ የሕግ ምሩቃንን በየቦታው እናያለንና ሊታሰብበት ይገባ ይመስለኛል፡፡

ከዚህም ባሻገር በአገራችን ያለው ሌላው ችግር የሙያና ሙያተኛ መተጣጣትም ጭምር ነው፡፡ በፌዴራል ፍርድ ቤት በአካውንቲንግ ተመርቃ የሕፃናትና ሴቶችን ጉዳይ የምትከታተል “የሕግ ባለሙያ” አውቃለሁ፡፡ እነዚህ የኅብረተሰብ ክፍሎች ለተደራራቢ ጥቃት የተጋለጡና የሕግ ባለሙያን ድጋፍ የሚሹ መሆናቸው ሲታሰብ ነገሩን ከገረሜታ ከፍ ያደርገዋል፡፡ በአማርኛና ሥነ ጽሑፍ ተመርቆ በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የምርመራ ክፍል ይሠራ የነበረ ሰውም አውቃለሁ፡፡ ይህንን ስል ግን ሙያዎችን እያጣጣልኩ እንዳልሆነ ይታወቅልኝ፡፡ ሙግቴ ለእነሱም፣ ለአገሬና ለአገራቸውም መልካም ነገ ነውና፡፡ በሁለተኝነት የማነሳው ጉዳይ በተለይ የሕግ ተማሪዎችን ብቻ የሚመለከት ሲሆን፣ ይኸውም በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ወቅት የኢሕአዴግ አባል እንዲሆኑ የሚደረግባቸው ጫና እንዲቆም የሚል ነው፡፡

ለምሳሌ የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ በአንድ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት በነበርኩበት ወቅት፣ ከክፍላችን ሃምሳ ሁለት ተማሪዎች የኢሕአዴግ አባል አንሆንም ብለን እንጀራችን ላይ የቆረጥን ተማሪዎች አራት ብቻ ነበርን፡፡ የዚህ ቀላሉ ምክንያት የሕግ ባለሙያዎችም እንደ ሌሎች ተማሪዎችና ዜጎች የፈለጉት ፓርቲ አባል ሊሆኑ የሚችሉበትን መብት ማክበር ቢገባም፣ ዳተኛ በሆንበት የዳኝነት ነፃነት ላይ ሌላ ሸክም ስለሚሆንና ፍርድ ቤቶቻችንን ፍትሕ አልባ ተቋማት ስለሚያደርግ ነው፡፡ በዋነኝነት ዳኞችንና ዓቃብያነ ሕጎችን የሚያሠለጥኑ የፍትሕ አካላት ማሠልጠኛ ማዕከላትም ተማሪዎችን ሲመዘግቡም ሆነ ሲፈትኑ፣ ከ10 እስከ 15 በመቶ ለአባልነት እየተሰጠ መሆኑ ሊቀርና ዕውቀትን ብቻ መሥፈርት ሊያደርጉ ይገባል፡፡

በተመሳሳይ አመክንዮ (Logic) አባልነት የሌሎችንም የፍትሕና የዴሞክራሲ ተቋማትን ሙያዊ ነፃነት እያሳጣ እንደሆነ መግለጽ ይኖርብኛል፡፡ ለዚህ ደግሞ ምሳሌ ከተባልኩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን፣ የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽንን፣ እንዲሁም እስካሁን ከጠቀስኳቸው የተሻለ እንቅስቃሴ ላይ ቢሆንም የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋምን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ምናልባት በቅርቡ ሜጄር ጄነራል ጻድቃን ገብረ ትንሳዔ እንዳሉት መልሶ በነፃነት መቋቋም የሚያስፈልጋቸውም ይመስለኛል፡፡ እነዚህ ተቋማት የእውነትና በእውነት የሚሠሩ ነፃ የሕግ ባለሙያዎችን የሚሹ ቢሆንም፣ መንግሥታችን ይህን ባለማድረጉና ማድረግም ባለመፈለጉ የሕዝብን ተዓማኒነት ማግኘትና የቆሙለትንም ዓላማ ማሳካት ሲሳናቸው ተመልክተናል፡፡

ብሶት ነውና ይለይለት አይደል?…… በአገራችን ተቋማት እንደ አዲስ ሲዋቀሩ ወይም የሆነ ዓይነት “አዲስ” አደረጃጀት ሲፈጠርና መዋቅር ሲሠራ፣ ነባር ሠራተኞችን የማንሳፈፍና ውስጣዊ መንገራገጭ የመኖሩ ነገር ተለምዶአዊ ነው፡፡ በቅርቡ እንኳን የአዲስ አበባ መንገድና ትራንስፖርት ባለሥልጣን ሠራሁት ባለው አዲስ መዋቅር ሳቢያ በርካታ ሠራተኞቹን ከመሥፈርት በታች ናችሁና አብረን አንቀጥልም ማለቱ አይረሳም፡፡ 

በነሐሴ 8 ቀን 2008 የወጣው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ የጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉን የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተርን ጠቅሶ ባወጣው ዘገባ፣ ተቋሙ ሲመሠረት በአፈጻጸማቸው ከፍተኛ ውጤት ያላቸው ዓቃቢያንን ብቻ መርጦና ተቋሙ ሊያስተናግድ የሚችለውን ያህል ብቻ ወስዶ በአዲሱ ተቋም ውስጥ እንደመደባቸው ተገልጾ ነበር፡፡ ታዲያ ለምን ለአዲስ ተቀጣሪዎች ማስታወቂያ ማውጣት አስፈለገ ለሚለው ጥያቄም፣ ዳይሬክተሩ አቶ ፋንታው አምባው ሲመልሱ “በየተቋሙ የነበሩትን ዓቃቢያንን ሁሉ እንድንወስድ የሚያስገድደን ሁኔታ የለም፤” ነበር ያሉት፡፡

እርግጥ ነው ሕጋችን ለእንደነዚህ ዓይነት አሠራሮች ግልጽ ምላሽ የለውም፡፡ ቢሆንም እንደ ፍትሕ ተቋም ተስፋ ስንጥልበት ገና ከመነሻው እንዲህ ዓይነት ግድፈት ውስጥ መግባቱ ይህ እምነታችንን የሚንድ ይሆናል፡፡ ነግ በእኔ ነውና የሙያ ጓደኞቻችን ጉዳይም ያሳስበናል፡፡ ይህ በሌላ አገላለጽ “የተንሳፈፉ” ወይም ሊንሳፈፉ የሚችሉ ሠራተኞች መኖራቸውን ቢነግረንም የ“ጥሩ አፈጻጸም” መለኪያው ብዙ ክሶችን ማቅረብ መቻል መሆኑን እንደሚያምነው የ“ፍትሕ ሚኒስቴር” ዓይነት አረዳድ፣ በፌዴራሉ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ውስጥ ከቀጠለ የተለወጠ ምንም ነገር አለመኖሩን የሚያስረዳ ነው የሚሆነው፡፡

ከዚህም ባሻገር የነባሮቹ ዓቃቢያን “ብቃት ማነስ” ጉዳይ እውነት ከሆነ ከፍተኛ የሕዝብ ተልዕኮና አደራ የተጣለባቸው፣ ግን ደግሞ ይህንን ሕዝባዊ አደራ ቀርጥፈው የበሉትን ሁለቱን ተቋማት (የኢፌዴሪ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽንንና የጉምሩክ ባለሥልጣንን) ብቃት የማጣት ገመና የሚገልጽና ተያያዥ ጥያቄዎችንም የሚያስነሳ ይሆናል፡፡ በመጨረሻም ይህን ልበልና ብሶት መር መልዕክቴን ላብቃ… የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት በአንቀጽ 29 ሥር ሐሳብን የመግለጽ ነፃነትን ቢደነግግም፣ ይህንን በመጻፌ ሥራ የማጣት ሥጋት አይኖርብኝም ማለት ግን አይደለም፡፡ የተጻፈ ሁሉ ቢተገበር ለዚህች አገር ሕገ መንግሥቱ ብቻ በቂዋ ነበር፡፡

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው ismaelu1432@yahoo.comማግኘት ይቻላል፡፡ 

 

Standard (Image)

ቀዳሚው የመንግሥት ዕርምጃ!

$
0
0

በሞገስ ሰለሞን

በአገራችን የተከሰቱትን መጠነ ሰፊ ሕዝባዊ የፖለቲካ ተቃውሞዎችን ቅጽበታዊ አድርጎ የመውሰድ አዝማሚያ በመንግሥት በኩል ይታያል፡፡ ከመንግሥት በኩል የሚሰጡት መግለጫዎችም ሆነ የአቋም ማብራሪያዎች ይህን ያትታሉ፡፡ በአገሪቱ የተቀጣጠለውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ኅዳር 2 ቀን 2008 ዓ.ም. በግንጪ ከተማ የተነሳበትን ጊዜ እንደ መነሻ አድርገን ብንወስድ ከአሥር ወራት በላይ የቆየ ‹‹የተጠየቅ መንግሥት ተጋፍጦ›› ሕዝባዊ አመጾችን ‹‹የውጭ ኃይሎች ሴራ›› በሚል የተመለከተበት መንገድ በአንድ በኩል፣ ለሕዝብ ተጠያቂ ያልሆነ መንግሥት ምን ያህል ከሕዝቡ መራቁን አመላካች ነው፡፡ በተለመደው መንገድ ሕዝብን በግልጽ በመሳደብ የተሰጡ መግለጫዎች (ሚኒስትሩ አቶ ጌታቸው ረዳ በተደጋጋሚ የሰጡዋቸው) ያለ ግልጽ ኃላፊነትና ተጠያቂነት ሚኒስትሩን ከሚዲያው ገሸሽ በማድረግ ተድበስብሰዋል፡፡ ይህም የሕዝቡን የተቃውሞ ጥንካሬ አመላካች እንጂ ገዥው ፓርቲ ያለውን የተጠያቂነት አሠራር በፍፁም አያሳይም፡፡ ተጠያቂነት ማለት በተለመደው መልኩ ከከፍተኛ ጥቅም (በኮድ ስሙ መጠነ ሰፊ የሕዝብ ሀብት ብክነት) ጋር የተያያዙትን የሥልጣን ወንበሮች ልቀማህ ነው በሚሉ የይስሙላ ማስፈራሪያዎች የሚገለጽ ሊሆን አይችልም፡፡

የዚህ የተቃውሞ መሠረታዊ መነሻ ከሆኑት ዋነኛ ምክንያቶች ውስጥ አንደኛው፣ የፖለቲካ መድረኩን ሕወሓት/ኢሕአዴግ በብቸኝነት የተቆጣጠረበት መንገድ ነው፡፡ ይህ መንገዱ የሕዝብን ድምፅ ማፈን፣ በሕዝቡ መካከል እኔ ከሌለሁ እንበታተናል ይባስ ብሎም እንጠፋለን እያሉ ሽብር መንዛት፣ አማራጭ የፖለቲካ ኃይል ለመሆን የሕዝብ ይሁንታን የሚያገኙ ግለሰቦችንም ሆነ የፖለቲካ ፓርቲዎችን በመከፋፈል ማዳከምና ማመንመን፣ ይህም ካልተሳካ በአገራችን የሕግ ታሪክ አምሳያ ባልተገኘለት የሽብርተኝነት ወንጀል የማፈኛ መሣሪያ ወደ ወህኒ መወርመር፣ የራሱም ሆነ ሕዝባዊ አቋም ያለውን ጋዜጠኛም ሆነ ነፃ አሳቢ ከሥራ ማባረር፣ ማጥፋትና ማሰርና ሌሎችንም ያጠቃልላል፡፡ በዚህ መልክ አገሪቱ የያዘችውን የፖለቲካና የሐሳብ እስረኛ የትየለሌ ቁጥር፣ በዚህም የደረሰውን ግፍና በደል በየዕለቱም የሚፈሰውን እንባ የሕዝቡ የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ የማረሚያ ቤቶች አሠራር በሙሉ እኔን ያየህ ተቀጣ ነው፡፡ አዲሱን ዓለም በቃኝ ቂሊንጦን ሆነ ነባሮቹ ታሳሪዎች ከቤተሰብም ሆነ ከጠያቂ እንዳገናኙ በጥበብ የተሠሩ ናቸው፡፡ በእነዚህ በተጠያቂ ጠያቂ የሰቆቃ ጩኸት መካከል በዓይን ብቻ ተያይቶ በእስከ አሁን በሕይወት መቆየትህን ለማየት አበቃን ለማለት ብቻ የቆሙ ናቸው፡፡

የሕዝብና የአገር ጉዳይ እኔንም ይመለከተኛል ብሎ ከገዥው ፓርቲ የተለየ አቋም መያዝ፣ በአጭሩ በምንና እንዴት በሆነ መልኩ እንደተዋቀረ በማናውቀው የስለላና የፖሊስ ኃይሉ ወጥመድ ውስጥ በደቂቃ መግባት ነው፡፡ ይህ የስለላ ኃይል ያለተግባሩ በሕዝቡ በራሱ ላይ የተዘረጋ ወጥመድ ሆኖ ሳለ ‹‹የደኅንነት ኃይል›› የሚል ምግባረ ሰናይ ስም ወጥቶለታል፡፡ የዚህ ወጥመድ ማነቆ ጠበቅ ሲል ላልቷል፡፡ በመጠኑ ላላ ሲልም ለሚዲያ ያልበቁትን ስም የለሾችን እልፍ አዕላፍ እስካሁን አንገታቸውን ቀፍድዶ ይዟል፡፡ ከዚህ ወጥመድ የተረፈው ደግሞ ከማንነቱ ከራሱ ጋር በክፉ ተጣልቶ በባዕድ አገር እንደ ከብት ለምግብ ብቻ ይኖራል፡፡ ባደግንበት የትኛውም ኅብረተሰብ ውስጥ ምግብ ከሰው ጋር የሚካፈሉት ፍቅር ለአብሮነት መሰባሰቢያ ምክንያት እንጂ፣ ለምግብነቱ መብላት እንደ ከፍተኛ ነውር ተቆጥሮ አድጎ ይህ የባዕድ  አገር አመንዣጊነት አገሩን፣ ሕዝቡንና ማንነቱን እያጣና እንዳጣ በቀን ሦስት ጊዜ እንዳይሸሽ አድርጎ እያስታወሰው ይሰቃያል፡፡ ታዲያ ስደተኛውስ ከእስረኛው አልባሰም? የዚህ ሁሉ ፖለቲካዊ ቀውስ ወደ ማኅበራዊ ቀውስ መሸጋገር ለወደፊቱም አብሮን የሚኖር ተጨማሪ ጠባሳችን እንደሆነ እሙን ነው፡፡

አሰቃቂው እስር በምን ምክንያት እንደሚመጣ ብዙ ጊዜ አደናጋሪ ነው፡፡ ማደናገሩ በማናቸውም ምክንያት ሊመጣ መቻሉ ነው፡፡ እዚህ ላይ በግልጽ በጠላትነት የታወጁትን ጋዜጠኝነትና ጋዜጠኞች በሙሉ የኦነግ፣ የመኢአድ፣ የኦብኮ ወይም የቀድሞው የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር አባል መሆንን ወይም መደገፍን ትተን ማለት ነው፡፡ በሃይማኖት ተቋም ውስጥ የሚነሱ ውስጣዊ ልዩነቶች ወይም የአስተዳደር ችግሮች ይፈቱ ማለት (በታላቁ አንዋር መስጊድና በአዲስ አበባ ልደታ ቤተ ክርስቲያን ያስታውሱዋል) በብዙኃኑ እስር ይቋጫል፡፡ በወባ ወረርሽኝ በክፉ ለተጠቁ ገበሬዎች ትኩረት ይሰጥ ማለት (1985) ወይም የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት መቀመጫ ከአዲስ አበባ/ፊንፊኔ ለማውጣት ሕዝብን አላማከራችሁም፣ ወይም በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የአካዳሚ ነፃነት ይከበር ፖሊስም ከግቢው ጥበቃነት ይውጣ ማለት በግፍ ለመታሰርና ለስቃይ ያጋልጣል፡፡

የተዋቀረው የፖለቲካ ሥርዓት ራሱ የዘረጋውን አሠራር ለእኛም ይገባል ማለት ለብዙኃን ሞት፣ እስርና ስቃይ ሰለባነት ይዳርጋል (ስለ ሲዳማ ክልል መሆን ጥያቄ በሐዋሳና አካባቢው የተደረገ ሠልፍ)፡፡ በማኅበራት ስም ተደራጅቶ መብትን መጠየቅ ምንም እንኳን ድርጅቱ የግል ቢሆንም እንኳን ወደማይቀረው እስር ይወስዳል፡፡ የልማት ድርጅት (ለምሳሌ ወንጂ ስኳር ፋብሪካ) ለሠራተኛው ደኅንነት ተገቢውን ጥንቃቄ ባለማድረጉ የደረሰውን ቋሚ የአካል ጉዳት መጠየቅ ከሥራ መታገድ ብሎም መታሰር ያስከተላል፡፡ አንድ ባህታዊ መንግሥትን ነቅፈዋል በሚል ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ መታሰሩን እየተቃወመ ከኑግ ጋር የተገኘ ሰሊጥ በሚል ፈሊጥ ከ13 የሚበልጥ ሰው ተገድሎና ብዙዎች ቆስለው በዚያ ሳያበቃ ሌሎች ታስረዋል (ጎንደር)፡፡ አስደንጋጩ ነገር ባህታዊው በወቅቱ ያለመታሰሩን ስናስብ የፖሊስ ኃይሉ ምን ነበር ዓላማው የሚል የማይመለስ ጥያቄን በውስጣቸን ትቶ ሄዷል፡፡

ሕግና የሕግ የበላይነት የማስፈን አሠራር ጥቅሙ ለሕግ አስከባሪው ራሱ መሆኑ ይዘነጋል፡፡ በአንድ ጥፋት/ክስ ድጋሚ ቅጣት መጣል የሕገ መንግሥቱ ክልከላ የመፍቀድ ድንጋጌ ይመስል፣ በድጋሚ በአንድ ጉዳይ መቀፍደድ የብዙዎቹ የፖለቲካ ፓርቲ አባሎችና መሪዎች ብሎም ጋዜጠኞች ዕጣ ፈንታ ሆኗል፡፡ ሥራ አጥነት በሕግ የተደነገገ የመታሰሪያ ወንጀል (አደገኛ ቦዘኔ በሚል) ሲሆን፣ ይህ ሕግ በ1997 ዓ.ም. ገዥው ፓርቲ የደረሰበትን የደጋፊ ማጣት ተከትሎ በወሰዳቸው ዕርምጃዎች መሻር ሲገባው አሁንም በሥራ ላይ አለ፡፡ ወገኖቻችን በባዕድ ምድር በሊቢያ ስለተገደሉ ቁጣን ለመግለጽ ሠልፍ መውጣት ከምክንያታዊ ጉዳዩ ጋር ተያይዥ የሆኑ መንግሥትን የሚመለከቱ ጥያቄዎች ቢነሱም እንኳን ለመታሰር ሰበብ ይሆናል፡፡

ታዲያ ይህ መጠነ ሰፊ የሕዝብ ተቃውሞ እነዚህ በማረሚያ ቤቶች ታጉረው የሚገኙ ሳይታሰሩም በተለያየ መልኩ በአፈናና በክትትል የሚኖሩ የነፃነት አርበኞቻችን ከፊል የትግል ውጤት ነው፡፡ ለሰላማዊ ትግል የከፈሉት አምሳያ የሌለው መስዋዕትነት፡፡ በመንግሥት ጭምር የሚዘከረውን የጦርነት አዙሪት መዘዝ ለአገር እንደማይበጅ ተረድተው ያልተሄደበትን መንገድ የቀየሱ ጀግኖቻችን ናቸው፡፡ አሁን ላለንበት ፖለቲካዊ ቀውስ መፍትሔው ውስብስብ፣ መንገዱ እጅግ ጠመዝማዛ ቢሆንም ጠቋሚና ቀዳሚ ዕርምጃው ግን ቀላል ነው፡፡ ሁሉንም የፖለቲካና የህሊና እስረኞች ከእስርና ክትትል መፍታት መንግሥት ጊዜ የማይሰጠው ቀዳሚ ዕርምጃ መሆን አለበት፡፡የሕዝብ ሐሳብ ሊታፈንና ሊታሰር እንደማይችል በታሪካችን ለአንዴና ለመጨረሻ የምንማርበት ምዕራፍ ሊሆን ይገባል፡፡ ፈጽሞ እንዳይደገም፡፡ ግለሰብና የፖለቲካ ቡድኖችን በማሰር የፖለቲካ አቋምን ለማመንመን የሚደረግ ጥረት (የኃይልና ግብታዊ ሥራ) በተቃራኒው የሰፊው ሕዝብ ሐሳብ ሁሉንም የሚመለከት ጉዳይ ሆኖ ይመጣል፡፡ በአጭሩ ጭቆና አብዮትን ይወልዳል፡፡

የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን መፍታት ወቅታዊና ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ የሚያደርገው፣ እነዚህ ሰዎች አሁን ላለንበት የፖለቲካ ቀውስ የሚኖራቸውን አዎንታዊ ተፅዕኖ በማሰብ መሆን የለበትም፡፡ ያ ተጨማሪና ወደፊት ለምናስባት የሁላችን ኢትዮጵያ የሚኖረው ፋይዳ በራሱ ቀላል የሚባል አይሆንም፡፡ ነገር ግን የቁምም ሆነ የዘብጥያ ታሳሪዎች መፈታት ያለባቸው የሐሳብ ልዩነቶች የሚስተናገዱባት አገር መወለድ ስላለባት ነው፡፡ የሐሳብ ልዩነቶች በጠመንጃና በጉልበት መስተናገድ ስለሌለባቸው ነው፡፡ የሐሳብ ልህቅና በጠመንጃ ብቻ መምጣት እንዳለበት የሚያሳዩና የሚጋብዙ አሠራሮችና አቋሞች ሁሉ አንዳዶቹ በሒደት አብዛኞቹ በፍጥነት መቀረፍ ስላለባቸው ነው፡፡ የሐሳብን ፋይዳ መመዘን ያለበት ሕዝብ እንጂ በሥልጣን ላይ የተቀመጠን አካል ጨምሮ ሌላ ማንም መሆን አይችልም፡፡ ይልቁንም የመንግሥት ዋነኛ ተግባር ግልጽና ላልተገደበ ሕዝባዊ ውይይቶች የመንግሥት የሚዲያ ተቋማትን ክፍት ማድረግ ነው፡፡ ይህ እስከ ገጠር ድረስ የወረደ ተቃውሞ ፈር እንደያዘ የለውጥ ኃይል በመሆን ሊጓዝ የሚችለው፣ እነዚህ የመንግሥት የሜዲያ ተቋማት ለሁሉም ሐሳብ እኩል ክፍት መሆን ሲችሉ ብቻ ነው፡፡

እስከ መቼ ለአገር ውስጥ ጉዳዮች በውጭ ባሉ የዜና አውታሮች ላይ ጥገኛ እንሆናለን? እስከ መቼስ የሚዲያ አውታሮች ከመዝናናት ባለፈ ይባስ ብሎ የወጣቱንና የሌላውን ዜጋ የማሰብ አቅም መስለቢያ ሆነው ይቀጥላሉ? ሰፋ ያለ አገራዊ ራዕይ በሚፈለገው መጠን አለመኖር ወይም እንዲኖረን ማድረግ ሌላ ነገር ሊሆን ይችላል፡፡ አገራዊ ሐሳቦቻችንን በበቂ ሁኔታ ምንም ያልበሰሉ ቢሆን በአንድ በኩል እንዲበስሉ አንዳችን ከሌላችን የምንማርበት መድረክ መፍጠር እንጂ፣ እነዚህን ከእኔ በላይ አዋቂ ላሳር በሚል መንፈስ ማንቋሸሽ መዳበር የሚገባው ሐሳብ እየቀጨጨና ሊቃና ወደማይችልበት ጠማማነት እየተቀየረ እንዲሄድ መንገድ ማመቻቸት ብቻ ይሆናል፡፡ እኔ እንደማስበው ሕዝባችን ታጋሽና ሆደ ሰፊ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ የማያውቀውን ሁሉ ለመማር፣ የሚያውቀውንም ለማጎልበት የማይታክት ባለ ብሩህ አዕምሮ ነው፡፡

ኅብረታችን በልዩነቶቻችን እንዲያብብ ከተፈለገ ምን ጊዜም መሥራት ያለብን መተማመን ያለበት ልዩነት እንዲኖር ከመሥራቱ ላይ ነው፡፡ ልዩነት ማለት በሙዚቃና በቋንቋ የሚገለጽ አይደለም፡፡ እነዚህ ለማንነታችን መሠረት የሆኑ ቁልፍ ነገር ግን አንዴ ከተረጋገጡ በኋላ ወደኋላ የማንመለስባቸው መሠረቶች ናቸው፡፡ ለ25 ዓመታት በመጀመሪያው ቀን በተረጋገጡ የማንነታችን መሠረቶች ላይ ስንዘፍን በመኖራችን ዋናው ሥራ ሙሉ በሙሉ ተዘንግቶ ቀርቷል፡፡

አሁንም ቢሆን መንግሥት የተቃውሞ ሠልፍ አድራጊዎችን ከማሰር ይህንም እንደ ሕግ ማስከበሪያ ዋነኛ መሣሪያ ከማድረግ መቆጠብ አለበት፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ወቅት ዋነኛው ሰላም ጠባቂ መሆን ያለበት ሕዝቡ ራሱ ነው፡፡ ያሉት አንዳንድ መጠነኛ የሰላም ችግሮች ሕዝቡን በማሳተፍ ሊቃለሉና ሊቀረፉ የሚችሉ ናቸው፡፡ የሕግ ማስከበር ሥርዓቱም ቢሆን በሰፊው ሊፈተሽ የሚገባው ነው፡፡ ተጠያቂነት የሌለበት የፖሊስ አሠራር ማለትም ሠልፈኛን በቆመጥና በጥይት መደብደብ ብሎም ማሰቃየት ተመልሶ እንደማይመጣ ማረጋገጫ ሊሰጥ ይገባል፡፡ ይህ ደግሞ የትዕዛዝ ፈጻሚው ፖሊስ ችግር ሳይሆን የአመራር ሰጪው እንደሚሆን አንጠራጠርም፡፡ ለመሆኑ አስለቃሽ ጭስ የሚባል ነገር ለአገራችን ፖሊስ አልተፈቀደም እንዴ? የከፋና ወደ አመፅ የሚሄድ ሠልፍ ነው ቢባል እንኳ እንደ ማንኛውም ዓለም የጎማ ጥይቶች የማንጠቀመው ለምንድን ነው? ሠልፎችስ እስከ መቼ የጦርነት አውድማ ይመስል በገዳይ ጥይቶች ይታጀባሉ?

መንግሥት የወቅቱን የፖለቲካ ሁኔታ አንገብጋቢነት ተገንዝቦ ዕርምጃዎቹ ሁሉ ማስተዋል የሚነበብባቸው ለወደፊቱ ሳይሆን፣ አሁኑኑ ከራሴ ውጪ የሚላቸውን የአገሪቱን ዜጎች በማማከር መጀመር አለበት፡፡ ወጣቱን እንዳማከረ ሰምተናል፡፡ ይህ ወጣት በኢሕአዴግ ሊግ የተደራጀ እሱ የሚፈልገውን ብቻ እንዲያወራ የተዘጋጀ ስለሆነ ዕርምጃውን ያቀጭጨዋል፡፡ የጋራ ጉዳይ የምንለው ሁሉ በተግባር የጋራ ይሁን፡፡

የፖለቲካና የሐሳብ እስረኞች በአስቸኳይ ይፈቱ!!

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው mogessol@gmail.comማግኘት ይቻላል፡፡ 

 

 

Standard (Image)

‘ጨው ሆይ ለራስህ ስትል ጣፍጥ አለበለዚያ…’

$
0
0

በመርሃጽድቅ መኮንን አባይነህ

ታዋቂው ናይጄሪያዊ ጸሐፊ ችንዋ አቸቤ “Things Fall Apart” በሚል ርዕስ እ.ኤ.አ.  በ1959 በእንግሊዝኛ ቋንቋ ጽፎ ያሳተመውን ዝነኛ መድበል የአገራችን ሰዎች ወደ አማርኛ ቋንቋ በመለሱበት ወቅት (ነገሮች ተሰባብረው ሲወድቁ) ብለውት እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ እውነቱን ለመናገር ለዚያ ርዕስ በግርድፉ የተሰጠው አቻ ትርጓሜ ትክክለኛነት ወይም ኢ-ትክክለኛነት አሁን ላይ ሆኜ ያን ያህል አብዝቶ አያስጨንቀኝም፡፡ ይሁን እንጂ በየትኛውም መስክ ቢሆን ነገሮች ከናካቴው ተሰባብረው እስኪወድቁና ደብዛቸው እስኪጠፋ መጠበቅ ወይም በቸልተኝነት እያዩ ማለፍ ፈጽሞ የሚመከር ጉዳይ እንዳልሆነ አጽንኦት ሰጥቼ ለማሳየት ብቻ፣ ለዚህ ጽሑፍ በመንደርደሪያነት ተጠቅሜበታለሁ፡፡

የመንደራችን ሰዎች ‘ውኃ ሲወስድ እያሳሳቀ ነው’ በማለት ልብሶቻቸውን እያወለቁ ለዋና ልምምድ ወደ አካባቢው ወንዞች የሚሯሯጡ ልጆቻቸውን ሲመክሩ እሰማ ነበር፡፡ ትዝ እንደሚለኝ በጣና ሐይቅ ዳርቻ ላይ ሆኖ ዋና የሚለማመድ ማንኛውም ሰው በእርግጥም ጥልቀት ወዳለው የውኃው ክፍል መግባት ከፈለገ ለዚሁ በሚያበቃው ቁመና ላይ የደረሰ መሆኑን ማረጋገጥ ነበረበት፡፡ ለጊዜው የቆመ መስሎት አጥጋቢ ችሎታ ሳይኖረውና በቂ ጥንቃቄ ሳያደርግ በውሱን አቅሙ እየተንበጫረቀ ወደ መሀል ለመዝለቅ ቢሞክር፣ በውኃው ኃይል ተገፍቶ የመውደቁንና ለሕልፈተ ሕይወት የመዳረጉን አደጋ ራሱ ሊያፋጥን ይችላል፡፡

እኔ እንደማምነው የመንግሥት ሥልጣንም ቀለል ተደርጎ ሲታይ ቀስ በቀስ እያሳሳቀ የሚወስድ ውኃን ይመስላል፡፡ ስለሆነም በልምምድ ያሉ ዋናተኞች ለጊዜው መዝናናታቸውን ብቻ ማዕከል አድርገው ላንዳፍታም ቢሆን ውኃውን በትክክል ከመቅዘፍ መዘናጋት የለባቸውም፡፡ አለበለዚያ ሥልጣን ፈጽሞ በእጅ ሊጨበጥ ወደማይችል አንዳች ፈሳሽ ነገር የመለወጥ አደጋ ስላለው፣ እንዳሰቡት ዋኝተውና ከውኃው ጋር የተፈጠረውን ግብግብ በቀላሉ አሸንፈው የመውጣት ዕድላቸው የመነመነ ይሆናል፡፡

በሰው ልጅ ጤናማ እንቅስቃሴ ውስጥ ዕድሎችና ፈተናዎች የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው፡፡ በመሆኑም ዕድሎችን ብቻ እየመረጡ በመጠቀም ፈተናዎችን ማንገዋለል አይቻልም፡፡ ይልቁንም ችግሮችን ፈርቶ ከሩቁ ከመሸሽ ወይም ከናካቴው መኖራቸውን ሽምጥጥ እያደረጉ ከመካድ ይልቅ የማሸነፊያውን ብልኃት ሰንቆ ፊት ለፊት መጋፈጡ እንደሚበጅ ይታመናል፡፡

ብዙኃኑ ኢትዮጵያዊያን አሁን አሁን አገራዊ ችግሮችን በውል ለይቶና ዙሪያ መለስ ምክሮችን በሚገባ አዳምጦ ለሕዝብ ጥያቄዎች በወቅቱ አመርቂ ምላሽ የመስጠት ሙሉ አቅም ያለው፣ ደፋር የሆነና በሕግ በተሰጠው ሥልጣን ተጠቅሞ ለሚያሳልፈው ውሳኔም ሆነ ለሚወስደው ዕርምጃ ኃላፊነት የሚወስድ ቁርጠኛ አመራር ያላቸው መስሎ አይሰማቸውም፡፡ እንዲያውም በሠለጠኑት አገሮች አዘውትሮ እንደሚከናወነው ነፃ የሕዝብ አስተያየት የሚጠየቅበት፣ የሚሰበሰብበት፣ የሚተነተንበትና መልሶ ለሕዝብ ይፋ የሚደረግበት ሳይንሳዊ አሠራር ቢኖር ዜጎች በገዛ መንግሥታቸው ያላቸው እምነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሸረሸረ መምጣቱን ማረጋገጥ እምብዛም የሚገድ አይመስልም፡፡ ከዚህ የአመራር ክፍተት (Leadership Deficit) የተነሳ ጥንቃቄ በጎደለው አካሄድ ወደ አስከፊ እንጦርጦስ እየወረድን መሆኑን ለመረዳት ነቢይ ሆኖ መገኘትን አይጠይቅም፡፡

እነሆ ይህ አነስተኛ መጣጥፍ በዋነኝነት የሚያተኩረው በአገር ላይ ያንዣበበውን አደጋ ለመቀልበስ ሕዝባችን ከመሪዎቹ በሚጠብቃቸው ትሩፋቶች ላይ ይሆናል፡፡ ያለጥልቅ ጥናትና ምርምር መሪነት በዚህ ጸሐፊ አስተያየት ከሁሉ በፊት ግንባር ቀደም ሆኖ በመሠለፍና ተከታዮችን እኩል በማነቃነቅ ለአንድ ለታለመ የጋራ ግብ ማብቃት ነው፡፡ በተናጠልም ተዋቀረ በቡድን የመሪነት ማዕከላዊ እሴቶች ደግሞ ቅንነት፣ ታታሪነት ወይም ትጋት፣ አርቆ አስተዋይነት፣ የማያወላውል ውሳኔ ሰጪነትና ራስን ለተከታዮች ዘላቂ ጥቅም አሳልፎ መስጠት ናቸው፡፡ እንዲያውም መልካም እረኛ የሚባለው ከራሱ ምቾት ይልቅ ለመንጎቹ ደኅንነት አጥብቆ የሚጨነቅ መሆን አለበት፡፡

መሪነት በአጭር ቃል ባላደራነት ነውና ሸክሙ ከባድና ፅናትን የሚጠይቅ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ መሪ ለመሆን በብዙኃኑ ዘንድ ተቀባይነት ማግኘት ያሻል፡፡ ለብዙኃኑ ፍላጎት ዋጋ የማይሰጥና የሕዝብን አመኔታ ያላተረፈ ማንኛውም ግለሰብ ወይም ቡድን ጥሩ መሪ መሆን አይችልም፡፡

ከዚህ ሀቅ ብንነሳ መሪነት በቁሙ ሲወሰድ ዕድለኝነት እንደሆነ አያከራክርም፡፡ አበው ‹‹ከሰው መርጦ ለሹመት ከእንጨት መርጦ ለታቦት›› ይሉናል፡፡ በአግባቡ ካልተያዘና ካልተሠራበት ግን የኋላ ኋላ በተመሪዎች ዘንድ ቅሬታን ማሳደሩና ሲብስም ተጠያቂነትን ማስከተሉ አይቀርም፡፡

‘አለባብሰው ቢያርሱ በአረም ይመለሱ’ ነውና አገራችን ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት አስተማማኝ ሰላምና መረጋጋት እየራቃት እንደመጣ ፈጽሞ መደባበቅ ወደማንችልበት ደረጃ ላይ ደርሰናል፡፡ ለዚሁ ሰላም መታጣትና ለግጭቶች መበራከት በሚሰነዘሩት መንስዔዎች ላይ ግን መንግሥትና ማኅበረሰቡ የሚሰጧቸው ምክንያቶች የተለያዩ ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ መንግሥት እነዚህን ደም አፋሳሽ ሁከትና ብጥብጦች በአመዛኙ ዕድገቱ የወለዳቸውና የሚጠበቁ ናቸው ሲል ይደመጣል፡፡ በእርግጥ ይህንን ድምዳሜ በቅጡ ማስረዳት ሳያዳግት አይቀርም፡፡ ድርጅታዊና መንግሥታዊ መግለጫዎች ደጋግመው እንደሚወተውቱት ልማትና ዕድገት ተጨማሪ ፍላጎቶችን እንደሚፈጥሩ በደምሳሳው ሊታመን ቢችል እንኳ፣ ከዚህ አልፎ ለምን ይህንን ያህል የአገራዊ ብጥብጥና ትርምስ መንስዔ እስከመሆን ሊደርስ እንደሚችል ግን ፈጽሞ ግልጽ አይደለም፡፡

ወደድንም ጠላንም በመሬት ላይ የሚታየውን እውነታ ስንከታተል ማኅበረሰቡ በዘላቂ የሰላም ጠንቅነት አዘውትሮ የሚያነሳቸው ቅሬታዎች ከፍ ብሎ የተጠቀሰውን አባባል የሚቃረኑ ናቸው፡፡ አሁን አሁን የማይናቅ ቁጥር ያላቸው ወገኖች ሕገ መንግሥቱ እንዳልተከበረ፣ በአገሪቱ ውስጥ የሕግ የበላይነት እንዳልተጠበቀ፣ የዜጎችና የሕዝቦች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችና ነፃነቶች ዘወትር እንደሚጣሱ፣ ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል እንደሌለና ሙስና ክፉኛ እንደተንሰራፋ እንደ ወትሮው በለሆሳስ ሳይሆን ድምፃቸውን ከፍ አድርገው በአደባባይ እያሰሙ ሲያማርሩ መስማት እንግዳ ነገር አይደለም፡፡

ይኸው ዘርዘር ሲል ደግሞ የውጭ ጉዳይ፣ የመከላከያ፣ የፖሊስና የደኅንነት መዋቅሩ በአንድ ዘር ብቸኛ ቁጥጥር ሥር እንደዋለ፣ የንግድና የኢኮኖሚ አውታሩም ተመሳሳይ ዕጣ እንደገጠመው፣ የአንዳንድ ክልሎች ፖለቲካዊ ድንበር ታሪካዊና ሕገ መንግሥታዊ መሥፈርቶችን ግምት ውስጥ ሳያስገባ ከደርግ ውድቀት በኋላ ወታደራዊ የበላይነት በነበረው ቡድን ፍላጎት ብቻ እንደተሰመረ በአማራ ክልል ብቻ የወልቃይት ጠገዴን፣ የሰቲት ሁመራን፣ የራያና አዘቦንና የመሳሰሉትን አካባቢዎች በምሳሌነት እየጠቀሱ በአድሎዓዊነት የተከናወነ ነበር የሚሉት ከአጎራባች ሕዝቦች መሬት በኃይል እየቀሙና እያስፋፉ የመከለል ዕርምጃ እንደገና እንዲከለስና እንዲታረም ተጨባጭ ችግሮችን በማሳያነት የሚያነሱ የማኅበረሰብ ክፍሎችም አሉ፡፡

እንግዲህ እነዚህንና የመሳሰሉትን የሕዝብ ቅሬታዎችና ስሞታዎች ጀሮ ዳባ ልበስ ብሎ ማለፍ ግዙፍ የመሪዎች ጉድለት ይሆናል፡፡ ከዚያ ይልቅ ጉዳዮችን በጊዜውና በወጉ እየተቀበሉ ማጣራትና ተፈላጊውን ውሳኔ መስጠት፣ በየትኛውም ደረጃ ላይ የሚገኝ አመራር የሚጠበቅበት ቁልፍ የሥራ ድርሻ ይሆናል፡፡ ይህ በብርቱ የኃላፊነት ስሜት ካልተከናወነ ግን (ያደረ ጉበት ወደ አጥንት ስላለመለወጡ) እርግጠኛ መሆን አይቻልም፡፡

ስለሆነም የታሪክ አጋጣሚ ፈቅዶላቸው በከፍተኛ የአመራር እርከን ላይ ያሉ የፖለቲካ ሥዩማን አገርና ሕዝብን ከአሳዛኝ ጥፋት ለማዳን ወይም ለመታደግ በግልም ሆነ በቡድን ደረጃ ትንሿን መስዋዕትነት ለመክፈል ፈጽሞ ማመንታት የለባቸውም፡፡ ይልቁንም መሪዎቻችን አገር ከጊዜያዊ የፖለቲካ ሥልጣን በላይ መሆኑን በውል መረዳት ይኖርባቸዋል፡፡ ቀድሞ ነገር አገር ከሌለ መንበረ ሥልጣን የሚተከልበትና ባንዲራ የሚውለበለብበት ሥፍራ አይኖርም፡፡ በዜግነት ስም የሚመራና በግብር ከፋይነት የሚተዳደር ሕዝብም እንዲሁ፡፡ ከሰው ልጅ የመማር ችሎታ ብዙ ጊዜ ያነሰ አቅም ያላት የዱር እንስሳ እንኳ የትኛውን እሾህ በቅድሚያ እናውጣልሽ ቢሏት ‘በመጀመሪያ የመቀመጫዬን’ አለች ይባላል፡፡ ቀሪውን እሾህ መሬት ከያዘች በኋላ ራሷ ልትለቅመው እንደምትችል ከወዲሁ በመተማመን ይመስላል፡፡

ከደርግ ውድቀት ማግሥት ኢሕአዴግ ለኢትዮጵያ ሕዝብ በርግጥ የሰላም፣ የዴሞክራሲና የልማት ጨው ሆኖ ብቅ ማለቱን ማንም ጨርሶ የሚዘነጋው አይደለም፡፡ ጨው ደግሞ ራሱ ምግብ ባይሆን እንኳ ዓይነተኛ የምግብ ማጣፈጫ ለመሆኑ አሌ የሚል ሰው የለም፡፡ እንዲያ ከሆነ ታዲያ ግንባሩ የመንግሥት ሥልጣን ከተቆናጠጠ በኋላ መሠረታዊ የጨውነት ባህርዩን መለወጥ ባልተገባው ነበር፡፡ እነሆ አሁንም ቢሆን ቢመሽ እንኳ አልጨለመበትምና ቢያንስ ለራሱ ሲል እንደ ቀድሞው መጣፈጡን መቀጠል ይኖርበታል፡፡ ይህ ሳይሆን የቀረ እንደሆነ ወትሮውኑም ቢሆን ያልደቀቀ አሞሌ ጨው በቅርፁ ድንጋይ ነውና ተፈላጊውን ጣዕም መፍጠር ካልቻለ እንደ ኮረት ተቆጥሮ በቀላሉ ሊጣል ወይም ሊወረወር ይችላል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ መሪዎቻችን ለጥቂት ቀናት ሱባኤ ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ ሲለያዩ በሚያወጧቸው ድርጅታዊ መግለጫዎች ታድሰናል ወይም ልንታደስ ነው እያሉ የገዛ ሕዝባቸውን ለመደለል ቢሞክሩ ‹‹የሞኝ ዘፈን ሁልጊዜ አበባዬ›› ይሆንባቸዋል፡፡

ከዚያ ይልቅ አሁን ከምንገኝበት ምስቅልቅል በአፋጣኝ ሊያወጣን ከፈለገ ኢሕአዴግ በሚመራው መንግሥት አማካይነት ቀጥሎ የተመለከቱትን ዕርምጃዎች መውሰድ ይጠበቅበታል፡፡

  • አገር ያወቃቸውንና ፀሐይ የሞቃቸውን ችግሮቻችንን ትክክለኛ ገጽታ ያለ ኃፍረት በመሸፋፈን እርስ በርሳቸው የሚቃረኑ መግለጫዎችን እያከታተሉ ከማውጣት ተቆጥቦ፣ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአገሪቱ ውስጥ በበርካታ አካባቢዎች በተለይም በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ውስጥ በተከሰቱት ደም አፋሳሽና አውዳሚ ግጭቶችና ብጥብጦች ሕይወታቸውንም ሆነ አካላቸውን ያጡትንና ሀብትና ንብረት የወደመባቸውን ዜጎች በኦፊሴል ይቅርታ ቢጠይቅ፣ አቅሙ እስከፈቀደ ድረስም በሁከቱ ከባድ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የመልሶ ማቋቋሚያ ድጋፍ ቢያደርግ፡፡
  • የወልቃይት ፀገዴ የአማራ ማንነት ይታወቅልን ንቅናቄ ኮሚቴ አባላትን ጨምሮ የመብት ጥያቄ አቅራቢዎች ወይም ሰላማዊና ሕጋዊ ተቃዋሚዎች ሆነው መንቀሳቀሳቸው የሚታወቅ ሆኖ ሳለ፣ የተለያዩ ታፔላዎች ያላግባብ እየተለጠፉባቸው ተይዘው ዘብጥያ የወረዱ ዜጎች የሰላሙን ሒደት ለማቀላጠፍ ሲባል ያላንዳች ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ ቢደረግና አቋሞቻቸውን በሕገ መንግሥቱ መሠረት እንዲያራምዱ ቢፈቀድላቸው፡፡
  • በፌዴራልም ሆነ በክልል መንግሥታት ይዞታ ሥር የሚገኙ መገናኛ ብዙኃን ሥራቸውን በነፃነት የሚያከናውኑበትና የሁሉም ወገኖች ድምፅ እኩል የሚሰማበት ምቹ ሁኔታ ቢፈጠር፡፡
  • በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት የፖለቲካ መጫወቻ ሜዳውን ክፍት አድርጎ ከአገር ውስጥም ሆነ ከባህር ማዶ ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር ለመገናኘት ቢፈቅድና የአገሪቱን መፃኢ ዕድል አስመልክቶ ታዋቂ ምሁራንን፣ የአገር ሽማግሌዎችንና የሃይማኖት መሪዎችን ጭምር ያሳተፈ ነፃና ግልጽ የብሔራዊ ዕርቅ ውይይት ቢጀምር፡፡

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው clickmerha1@gmail.comማግኘት ይቻላል፡፡ 

 

 

 

 

Standard (Image)

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የአቤቱታ መርሐ ግብርና ተደራሽነት በአዲስ አበባ የፈጠረው ጫና

$
0
0

በስመኘው አራጌ ይትባረክ

አዲስ አበባ ከተማ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ተዋልደውና ተቀላቅለው የሚኖሩበት የፌዴራል መንግሥቱ መቀመጫ በመሆኗ፣ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ያለመፈራረጅ በእኩልነት የሚኖሩባት የመቻቻል ከተማ ናት ለማለት ይቻላል፡፡ በዚያው አንፃር የሕግ የበላይነት ካልተረጋገጠ፣ ሥርዓትና ደንብ ካልተከበረባት፣ ዜጎች በእኩልነትና በፍትሐዊነት የማይስተናገዱባት ሁኔታ ከተፈጠረ የዚያኑ ያህል አስፈሪ ከተማ ነች፡፡

በመሆኑም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም ሆነ የፌዴራሉ መንግሥት የከተማዋ ሰላምና ፀጥታ እንዳይናጋና ፍትሕ እንዳይጓደል፣ ዜጎች በየአካባቢያቸው ፍትሕ ማግኘት እንዲችሉ አስተዳደራዊና ሕጋዊ ሥራዎችን በትጋት ለመሥራት ጥረት ማድረጋቸው የግድ ነው፡፡ በከተማዋ ከአንዱ ጫፍ ወደ ሌላው ሄዶ ጉዳይ ለማስፈጸምና ሥራ ለመሥራት የትራንሰፖርት እጥረትና የኢኮኖሚ አቅም ውሱንነት ዜጎችን የሚፈታተኑ ጉዳዮች መሆናቸው የታወቀ ነው፡፡

እነዚህን ችግሮች ለመቋቋም ይቻል ዘንድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአሥር ክፍላተ ከተሞች ተዋቅሮ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ አስተዳደራዊና ሕጋዊ አገልግሎቶችን ዜጎች በየአካባቢያቸው እንዲያገኙ እንቅስቃሴ ከተጀመረ ጥቂት የማይባሉ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ሁሉንም የአገልግሎት ዓይነቶችና የአገልግሎት አሰጣጥን ለመገምገም ወይም አስተያየት ለመስጠት አይደለም፡፡ ዜጎች ፍትሐዊ አገልግሎት እንዲሰጡ የተዋቀሩትን ፍርድ ቤቶች ለመመልከት ነው፡፡

በዚህ የፍርድ ቤቶች አወቃቀር በፌዴራል የመጀመሪያና ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የአቤቱታ መስተንግዶ አሰጣጥና የተደራሽነት ጉዳይ ላይ ይህንን መጣጥፍ ለማቅረብ ወድጃለሁ፡፡ በአሁኑ ጊዜ ፍርድ ቤቶች ዕረፍት ላይ ስለሆኑ ያለፈውን ዓመት ሥራቸውን የሚገመግሙበት ወቅት ነው፡፡ ይህ ጽሑፍም በአብዛኛው የሚያተኩረው ያለፈውን ዓመት አሠራር ነው፡፡

የአቤቱታ መርሐ ግብር

በፍርድ ቤቶች አሠራር ዜጎች መብታቸውን ከሚያስከብሩባቸውና የክርክር ሒደቱን ለማሳካት ወይም ለማስቆም ከሚጠይቋቸው አገልግሎቶች አንዱ አቤቱታ  ነው፡፡ አቤቱታ ከመደበኛው ክርክር ውጪ ተከራካሪ ወገኖች አስቸኳይ ጉዳይ ሲያጋጥማቸው  ለፍርድ ቤት በማቅረብ ሕጋዊ መፍትሔ የሚገኙበት ሕጋዊ አሠራር ነው፡፡ ከዚህ አንፃር የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች አስተዳደራዊ ሥራቸውን፣ የሚሠሯቸውንና አቤቱታ ለመቀበል መርሐ ግብራቸው የሚቀርፀው በፕሬዚዳንቶች በሚመራው መዋቅር እንደሆነ ይታመናል፡፡ በዚህ መሠረት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያሉት የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች አቤቱታ የሚቀበሉበትንና የሚያስተናግዱበትን ቀን መርሐ ግብር በመንደፍ ለፍትሕ አካል አጋዥ ለሆኑት ዓቃቤ ሕግ፣ ጠበቆች፣ የሕግ ሙያ አገልግሎት በነፃ ወይም በክፍያ ለመስጠት ፈቃድ ላላቸው አካላት አመቺ ሁኔታ መፈጠሩን ማረጋገጥ አለበት፡፡

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች ማስቻያ ሥፍራዎቸን ስንመለከት አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ምድብ፣ የቀድሞው ጳውሎስ ምድብ፣ አውቶብስ ተራ አዲሱ ሚካኤል ፊት ለፊት በግምት ወደ ውስጥ 200 ሜትር ገባ ብሎ ይገኛል፡፡ የጉለሌ ክፍለ ከተማ አምስት ኪሎ ብሔራዊ ሙዚየም ፊት ለፊት የድሮ መናገሻ አውራጃ ግቢ ውስጥ መናገሻ ምድብ ችሎት በመባል በሚታወቅ ግቢ ያስችላል፡፡ የየካ ክፍለ ከተማ ደግሞ ሾላ ገበያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በራሱ ሕንፃ ላይ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ የቦሌ ክፍለ ከተማ ምድብ ችሎት ሲኤምሲ ሰሚት መንገድ ማና ሕንፃ አለፍ ብሎ ራሱ ባስገነባው ሥፍራ አገልግሎቱን ይሰጣል፡፡ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቂርቆስ ምድብ ቄራ ራሱ ባሠራው ሕንፃ በማስቻል ላይ ይገኛል፡፡ ልደታ በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ግቢ ውስጥ ራሱ ባሠራው ሕንፃ አገልግሎቱን በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ ኮልፌ ቀራኒዮ ጦር ኃይሎች አካባቢ በቅርቡ በተከራየው ሕንፃ ላይ ያስችላል፡፡ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ጎፋ ገብርኤል ማዞሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ባለ የኪራይ ሕንፃ ላይ አገልግሎቶችን ይሰጣል፡፡ አቃቂ ቃሊቲ መናኸሪያ አለፍ ብሎ ራሱ ባሠራው ሕንፃ ላይ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

የአሥሩንም ክፍላተ ከተሞች የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች ማስቻያ ሥፍራ ያለምክንያት አልተጠቀሱም፡፡ የሁሉም ችሎቶች የአቤቱታ ማስተናገጃ ቀን በአብዛኛው አንድ ቀን በሚሆንብት ጊዜ ለፍትሕ አጋዥ የሆኑ ከላይ የጠቀስኳቸው አካላት እንዴት እንደሚቸገሩ ልብ በሉ፡፡ በተግባርም እንደሚታየው ባለፈው ዓመት የአብዛኞቹ ችሎቶች የአቤቱታ ቀን መቀበያ ረቡዕ እንደነበረ የዚህ መጣጥፍ ጸሐፊ መረዳት ችሏል፡፡ ስለዚህ ከላይ የፍትሕ አካላቱን ያግዛሉ ተብለው የተቋቋሙ አካላትንና የፍርድ ቤት ተገልጋዮች በአሥሩም ክፍላተ ከተሞች ጉዳይ ሲኖራቸው ከየትኛው ሊሆኑ ይችላሉ? ይህንን የአቤቱታ ቀን በአንድ ቀን ሁሉም ችሎቶች እንዲያስተናግዱ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት በሚወጣ መርሐ ግብር ሊተዳደር ይገባል፡፡

በዚህ የአቤቱታ ቀን መደራረብ ምክንያት ዜጎች መብታቸውን ሊያጡባቸው የሚችሉባቸው ሁኔታዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ አንድ የጥሬ ገንዘብ ወጪ የሚደረግበት ባለ ጉዳይ የዕግድ አቤቱታ በማቅረብ የሚሸሸውን ይህንን ገንዘብ ወይም ሌላ ንብረትን ለማስቆም ረቡዕ መጠበቅ ካለበት፣ በሁለት ችሎቶች አስቸኳይ አቤቱታዎች ቢኖሩት አንዱን የማጣት ችግር ያጋጥመዋል ማለት ነው፡፡ ስለሆነም ለእነዚህ ችሎቶች በአንድ ከተማ ውስጥ ያሉት ቢያንስ በሳምንት ያሉትን አምስት ቀናት ሊደለደሉባቸው ይገባል የሚል እምነት አለኝ፡፡

የተደራሽነት ጉዳይ

ፍርድ ቤቶች በሥረ ነገርና በክልል የዳኝነት ሥልጣን የሚከፋፈሉበት ዋና ዓላማ ለኅብረተሰቡ ፍትሕ ተደራሽ እንዲሆን ለማድረግ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ ዜጎች በአካባቢያቸው ፍትሕ እንዲያገኙ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአሥር ክፍላተ ከተሞች የተዋቀሩት የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች ሁሉንም የችሎት ዓይነቶች አሟልተው ሊይዙ ይገባል፡፡ በተግባር እንደሚታየው ግን ሁሉም ችሎቶች ሁሉንም የክርክር ጉዳዮች አሟልተው ሲሰጡ አይታይም፡፡ ይህም ሲባል አሁን ባለው የፍርድ ቤቶች አወቃቀር የፍትሐ ብሔር፣ የቤተሰብ፣ የሥራ ክርክር፣ የወንጀል ችሎቶችና የአፈጻጸም ችሎቶች በአንድ ፍርድ ቤት ተሟልተው አይገኝም ማለት ነው፡፡ ለምሳሌ የአቃቂ ቃሊቲ ምድብ ችሎት ፍርድ ቤቶች የሰጡትን ውሳኔ ፍርድ ለማስፈጸም ቂርቆስ ምድብ ችሎት የአፈጻጸም ፋይል መክፈት አለባቸው፡፡ ይህ ፍርድ ቤት የሚገኘው ቄራ አካባቢ ሲሆን፣ ይህ ከመደበኛው ክርክር ባልተናነሰ ጊዜና ገንዘብ የሚጠይቀው አፈጻጸም ችሎት በአቃቂ ቃሊቲ አለመከፈቱ፣ በተከራካሪ ወገኖች ላይ የሚደርሰውን እንግልት ተገልጋዮች ሊገምቱ ይችላሉ፡፡ ከተደራሽነት አንፃር ይህ ተገቢ አይመስልም፡፡

በተመሳሳይ መንገድ የቦሌና የየካ ምድብ ችሎቶች የሰጧቸውን ፍርዶች አፈጻጸም የሚከፍተው በአራዳ ምድብ ችሎት ነው፡፡ ይህም በተመሳሳይ መንገድ ተገልጋዮችን ለእንግልት የሚዳርግ አሠራር ሆኖ ይታያል፡፡ የአራዳው አፈጻጸም ችሎት፣ የየካ፣ የአራዳ፣ የመናገሻ፣ የቦሌ የሰጧቸውን ፍርዶች ለማስፈጸም በአንድ ዳኛ ላይ የሚፈጠረውን የሥራ ጫናም ልብ ይሏል፡፡ በዚህ ምክንያት በአፈጻጸም ላይ የሚመደቡ ዳኞች የመሰላቸትና ከሥራው ጫና አንፃር ባለጉዳዮችን በተገቢው መንገድ ለማስተናገድ ሲቸገሩ ይታያል፡፡

በአፈጻጸም ችሎት ሌላ መደበኛ ክርክር የማያስተናግዱ ችሎቶችም አሉ፡፡ ለምሳሌ የቦሌ ምድብ ችሎት ከቤተሰብና ከሥራ ክርክር ውጪ ያሉትን የውል፣ የውርስ፣ የንግድ፣ የሁከት ይወገድልኝ ክርክሮች አያስተናግድም፡፡ መንግሥት በከፍተኛ ወጪ አዳዲስ ሕንፃዎችን የገነባው የፍትሕን ተደራሽነት በማረጋገጥ ዜጎች ሁሉንም የሕግ ጉዳዮች በአቅራቢቸው ማግኘት እንዲችሉ ነው፡፡ በተለይ በአዲስ አበባ ደረጃ ሁሉንም አገልግሎቶች አንድ ዕርምጃ በተራመዱ ቁጥር ገንዘብ ወሳኝ በሆነበት ክልል፣ ዜጎች ፍትሕን በአቅራቢያቸው እንዲገኙ ማመቻቸት በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡ ስለሆነም የሁሉም ፍርድ ቤቶች ችሎቶች ሁሉንም የክርክር ዓይነቶች አሟልተው ሊሰጡ ይገባል፡፡

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤቶችም ያለው የተደራሽነት ችግር ተመሳሳይ ነው፡፡ በ2008 ዓ.ም የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች በአራት ማስቻያ ሥፍራዎች ተዋቅረዋል፡፡ ኮልፌ ቀራኒዮ፣ ልደታ፣ ቂርቆስና ንፋስ ስልክ ላፍቶ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሚስተናገዱ ሲሆን፣ የአዲስ ከተማና ጉለሌ ክፍለ ከተሞች በአራዳ ሰባራ ባቡር አካባቢ የማስቻያ ሥፍራ ይስተናገዳሉ፡፡ የካና የቦሌ ክፍላተ ከተሞች ደግሞ በቦሌ ምድብ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አገልግሎቱን እንዲሰጡ ተዋቅረዋል፡፡ አቃቂ ቃሊቲ ደግሞ በአቃቂ ቃሊቲ አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ይሁን እንጂ ቀጥታ ክስ የሚባለውን ችሎት ከልደታ ፍርድ ቤት ውጪ ሌሎች አይሰጡም፡፡ ይህም አንደኛው የተደራሽነት ችግር ነው፡፡ ፍርድ ቤቶች በአንድ ማስቻያ ሥፍራ መከማቸታቸው በራሱ የሚያመጣውን ችግርም ልብ ይሏል፡፡ ባለፈው ዓመት ከፍተኛው ፍርድ ቤት በዓመት ሁለት ጊዜ ብቻ ይቀጥር እንደነበር ሁላችንም የምንገነዘበው ጉዳይ ነው፡፡ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንድ የቼክ ጉዳይ ከሁለት ዓመት በላይ መውሰዱን የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ በግሉ ምስክር ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት የዘገየ ፍትሕ ሊከሰት የሚችለው ከመዝገቦች መብዛት፣ ሌሎች የተቋቋሙ ችሎቶች ተመሳሳይ አገልግሎት ለመስጠት ባለመቻላቸውና በአንድ ችሎት በርካታ ጉዳዮች በመከማቸታቸው ነው፡፡ ስለሆነም ተደራሽነት ዜጎች ከሚማረሩባቸው ጉዳዮች አንዱ ስለሆነ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትም ሆነ፣  በከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የተቋቋሙት ችሎቶች ሁሉንም የችሎት ዓይነቶች አሟልተው ሊሰጡ ይገባል፡፡

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊው በፌዴራል ማናቸውም ፍርድ ቤት ጠበቃና የሕግ አማካሪ ናቸው፡፡ ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው addisprofessionaltranslation@gmail.comማግኘት ይቻላል፡፡ 

 

 

Standard (Image)

ሃያ ስድስት አሮጌ ዓመታት

$
0
0

በመታሰቢያ መላከ ሕይወት ገብረ ክርስቶስ

በጣም እርግጠኛ ሆኜ መናገር የምችለው ነገር ቢኖር ማንም ኢትዮጵያዊ አዲስ ዓመት ሲመጣ አንድ ሰው ወይም ከዚያ በላይ መልካም አዲስ ዓመት የምትለዋን መልካም ምኞት ሳይናገር ያልፋል የሚል እምነት የለኝም፡፡ ነገር ግን ዓመት በተለወጠ ቁጥር አስደንጋጭ የኑሮ ውድነትና ለኑሮ የማይመቹ ዜናዎች መስማት በእጅጉ የተለመዱ ናቸው፡፡ የቤት ኪራይ መናር፣ የዋጋ ግሽበት፣ የሰላም መታጣት፣ ወዘተ አዲሱን ዓመት የደስታና የብልፅግና ከማድረግ ይልቅ ፍርኃት እንዲይዘንና እንድንሸማቀቅ የሚያደርግበት ሁኔታ መቆሚያ ማግኘት አልቻለም፡፡

በ2008 ዓ.ም. አገሪቷ ያስተናገደችው ሕዝባዊ አመፅ የብዙ ሺሕ ሰዎችን ሕይወት በእጅጉ ያናጋ ሆኖ አልፏል፡፡ ይህንን ችግር በእጅጉ ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ ተመልክተንና አጥንተን እውነተኛ ሰላምን ማግኘት እንድንችል መጣር፣ ከማንኛውም አገሩን ከሚወድ ዜጋ የሚጠበቅ ተግባር ነው፡፡ እዚህ ላይ ልንገነዘበው የሚገባ ተግባር እውነተኛ ሰላምን ምን እንደሆነ ማወቅ ስንችል ነው፡፡ በጠመንጃና አፈሙዝ የመጣ ሰላም ሰላም ሊባል አይችልም፡፡ ከኢኮኖሚ ዕድገት ጋር፣ ከሰብዓዊ፣ ከቁሳዊ፣ ከዴሞክራሲያዊ መብቶች፣ ወዘተ ጋር ሲመጣ ብቻ ነው እውነተኛ ሰላም ሊባል የሚቻለው፡፡

እንደሚታወቀው በአንድ መንግሥት ላይ የሚነሳ ተቃውሞ በአራት የሚከፈል ነው፡፡ በመጀመሪያ አንድ መንግሥት የተሳሳተ መንገድ ይዞ ሲጓዝ ድምፃቸውን የሚያሰሙት የአገሪቱ ምሁራን ናቸው፡፡ ከዚያም በመቀጠል ሚዲያው የተቃውሞ መንደር ይሆናል፡፡ በሦስተኛ ደረጃ ሥርዓቱ ውስጥ የነበሩ ሥርዓቱን ለማረምና ለማሻሻል ጥረት አድርገው አልሳካ ሲላቸው ከሥርዓቱ ወጥተው ተቃዋሚ የሚሆኑበት ሒደት ነው፡፡ በመጨረሻም ሥርዓቱ የሚያራምደው ትክክለኛ ያልሆነ መንገድ የእያንዳንዱን በር ማንኳኳት ሲጀምር ሰፊው ሕዝብ (በአብዛኛው ያልተማረው የኅብረተሰብ ክፍል) አንዲት ትንሽ ሰበብ ፈልጐ አደባባይ መውጣት ይጀምራል፡፡

በዚህን ወቅት ነው የሥርዓቱ መሪዎች ብቃት የሚለካው፡፡ በብዙ አገሮች እንደታየው ሕዝባዊ አመፅን በጠመንጃ አፈሙዝ ለማስቆም የሞከሩ ራሳቸውንም አገራቸውንም ለውድመት ነው የዳረጉት፡፡ መፍትሔ የሚሆነው ማንኛውንም ዓይነት ሕገ መንግሥታዊ፣ ርዕዮተ ዓለማዊና ፖሊሲያዊ ፈጣን ለውጥ በማምጣት ብቻ ነው ያንን ሥርዓት ማዳን የሚቻለው፡፡ በዓለማችን የአመፆች ታሪክ ሚኒስትሮችንና ሌሎች ባለሥልጣናትን በመቀየር የተረፈ አንድም ብልሹ ሥርዓት የለም፡፡ ምክንያቱም እነዚያን ብልሹ ባለሥልጣናት የፈጠረው ብልሹ የሆነው ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት በመሆኑ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እነዚህን ሰዎች አምጦ የወለዳቸው ሥርዓቱ በመሆኑ ነው፡፡

እዚህ ላይ እንደ አንድ ዜጋ በአገራችን ያለው ዋና ችግር ምንድነው የሚለውን ጉዳይ ብዕሬን ከማንሳቴ በፊት፣ ከብዙ ምሁራንና ከአንባቢያን ጋር ውይይት አድርጌ የደረስኩበት አንድ ድምዳሜ አለኝ፡፡

አገራችን ኢትዮጵያ እንደሚታወቀው ሰፊ በመሆኗ በተለያዩ ቦታ የተለያየ የሁከት መጠን፣ ችግሮችና ተግዳሮቶች እንዳሉ ለሁሉም ግልጽ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ በኢትዮጵያ ውስጥ (ከዚህ ቀደም በሪፖርተር ጋዜጣ ለማመልከት እንደሞከርኩት) የተለያየ የፌዴራል ሥርዓት መኖሩ አንዱ ክልል ለልማትና ለኢቨስትመንት አመቺ ሲሆን ሌላው ደግሞ መንደርተኝነት ጠባብነት የሚንፀባረቅበት በመሆኑ፣ ለልማትና ለኢንቨስትመንት አስቸጋሪ ይሆናል፡፡ ባለፉት 25 ዓመታት በአገራችን የታየው ጉርብጥብጥ ያለ ዕድገት በተለይ አሁን ላይ አንዱን ተጠቃሚ ሌላውን ቀላዋጭ እያደረገ በመሆኑ፣ አሁን ላለው ብጥብጥና አለመረጋጋት እንደ ዋና ምክንያት አድርጐ መውሰድ ይቻላል፡፡

ሌላው ደግሞ መብትን በተመለከተ እንደ አዲስ አበባ ባሉ ከተሞች አንድ ዜጋ የቤት ባለቤት የመሆንና ቤቱን የማከራየት ከዚያም በላይ የመሸጥ መብት ሲኖረው፣ የገጠሩ ማኅበረሰብ ግን ያለው መብት መሬቱን ማረስና ማከራየት ብቻ ነው፡፡ የብሔር ብሔረሰቦች መብት እስከ መገንጠል የሚል ሕግ ያወጣ መንግሥት እንዴት መሬት የመሸጥ መብት ይከለክላል? አንድ ገበሬ ዕድሜው በሚደክምበት ጊዜ መሬቱን ሸጦ ወደ ከተማ ሄዶ ቀለል ያለ ሥራ እየሠራ የመኖር መብቱን ሕገ መንግሥቱ አግዶታል፡፡

ለምሳሌ አንድ ገበሬ አሥር ልጆች ቢኖሩትና ሁለት ሔክታር መሬት ቢኖረው፣ ገበሬው ዕድሜው ሲገፋ መሬቱን ለልጆቹ ሲያከፋፍል በመሬት መጣበብ ሳቢያ ሁሉም ድሆች ነው የሚሆኑት፡፡ ነገር ግን ይህ ገበሬ መሬቱን ለባለ ሀብት ሸጦ የተወሰነ ገንዘብ ቢያገኝ፣ ባለሀብቱ መሬቱን አልምቶ ለገበሬው ልጆችና ለአካባቢው ወጣቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ በዚያ አካባቢ ያልነበሩ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችንና ልማቶችን የሚያመጣ በመሆኑ፣ መንግሥት ወደ ሌሎች ጉዳዮች ፊቱን እንዲያዞር ይረዳዋል፡፡

ኢትዮጵያ እንደ ጐረቤቶችዋ በረሃማ የሚበዛባት አገር ሳትሆን አብዛኛው የአገሪቱ መሬት ሊታረስና ለተለያዩ ልማቶች ሊውል የሚችል በመሆኑ፣ ላለፉት ዓመታት ዋና ትኩረታችን በዚህ ዘርፍ ላይ አለማድረጋችን አሁን ለምናየው አለመረጋጋት ዋነኛው ችግር ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ሥልጣን የያዘው ኃይል በገጠሪቷ ኢትዮጵያ ለሰፋፊ እርሻዎች (Commercial Farming) ቤተሰባዊ እርሻ (Substantial Farming) የሚሆነውን መሬት በካርታ ደረጃ በመለየት ሰፊ ሥራ መሥራት ቢገባውም፣ ይህንን አለማድረጉ ትልቅ ጉድለት ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ተራራማ ቦታዎች ለቤተሰብ እርሻዎች፣ ሜዳማ ቦታዎች ለሰፋፊ እርሻዎች ተብሎ መለየቱ እጅግ ወሳኝ ሥራ ነው፡፡ ሌላው ትልቅ ችግር ነው ብዬ የማምነው በሕገ መንግሥቱ ላይ የመሬትን ባለቤትነት ለመንግሥት ብቻ ማድረግ የሚያስከፍለው ዋጋ አደገኛ መሆኑ ነው፡፡

በእኔ እምነት መሬት በአምስት ባለቤቶች ተከፍሎ መተዳደር አለበት፡፡

  1. የፌዴራል መንግሥት የሆነ የመሬት ይዞታ

ይህ ዓይነት ይዞታ የፌዴራል መንግሥት ለተለያዩ ተግባራት ማለትም እንደ ብሔራዊ ፓርኮች፣ ታላላቅ የባቡርና የመንገድ ልማቶች የሚገነቡባቸው መሬቶች፣ የዩኒቨርሲቲዎች፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ የወታደራዊ ተቋማት፣ የኤርፖርቶች፣ ወዘተ የመሳሰሉ የመሬት ይዞታዎች የፌዴራል መንግሥት ይዞታ ሆነው መያዛቸው በእጅጉ ተገቢ ነው፡፡   

  1.  የክልል መስተዳድሮች የሚያስተዳድሩት መሬት

ይህ ዓይነቱ መሬት ለትምህርት ቤቶች፣ ለስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ ለፓርኮች ወዘተ የሚያገለግሉ የሚሆኑ ይዞታዎች በክልል መስተዳደሮች በባለቤትነት ቢተዳደሩ በእጅጉ የተሻለ ነው፡፡ 

  1. በግለሰብ የሚያዙ መሬቶች 

ማንኛውም ዜጋ የከተማም ሆነ የገጠር ነዋሪ የእኔ የሚለውና በማንኛውም ጊዜ ሊያለማው፣ ሊያከራየው፣ ሊሸጠውና ሊለውጠው የሚችለው የመሬት ይዞታ ባለቤት ሊሆን ይገባል፡፡ የማንኛውም ዜጋ የዜግነት መብት ከመሆኑም በላይ ሰብዓዊና ቁሳዊ መብት በመሆኑ ይህ መብት ያለ ምንም መሸራረፍ መከበር አለበት፡፡ እያንዳንዱ ዜጋ ለአገሩ ዕድገት በያዘው ይዞታ ላይ ተግቶ የሚሠራውና በራስ መተማመን የሚጨምረው፣ የባለቤትነት መብት ያለምንም መሸራረፍ ሲከበር ብቻ ነው፡፡ በእኔ እምነት አሁን ለሚታየው አለመረጋጋት ይህ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው ብዬ አምናለሁ፡፡   

  1. በማኅበረሰብ ተቋማት የሚያዝ መሬት

የሃይማኖት ተቋማት፣ እድሮች፣ አክስዮን ማኅበራት፣ ወዘተ የብዙኃን ንብረት የሆነ የመሬት ይዞታ ነው፡፡    

  1. በዓለም አቀፍ ተቋማት የሚያዝ መሬት 

ኤምባሲዎች፣ እንደ ተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ አፍሪካ ኅብረት ያሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት የሚያዙ የመሬት ይዞታዎች ሲሆኑ፣ በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት መሬት የመንግሥትና የሕዝብ ነው ይላል እንጂ፣ እነዚህ የመሬት ይዞታዎች መንግሥትም ሆነ ሕዝብ ሊያዝባቸው የማይችሉ ይዞታዎች ናቸው፡፡

በዚህ መንገድ ሕገ መንግሥቱ ቢስተካከል ሁሉም የመሬት ባለቤት ኖሮት ተገቢውን እንክብካቤ የሚያገኝ በመሆኑ በአገሪቱ ውስጥ ፈጣን ዕድገትንና ሰላምን ማየት ይቻላል፡፡ ምክንያቱም አብዛኛው ዜጋ ጊዜውን በሥራ ስለሚያሳልፍ ለፖለቲካ የሚሆን ጊዜ እምብዛም አይኖረውም፡፡

እንደሚታወቀው በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፓርክ ለመገንባት እየሞከረች ስትሆን፣ ለዚህ ልማት ትልቁ ግብዓት ኤሌክትሪክ ወይም የሰው ኃይል ሳይሆን፣ የፋብሪካ ሠራተኛ ሊገዛው የሚችለው ዝቀተኛ ዋጋ ያለው ምግብ ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሚገኘው ከሰፋፊ እርሻዎች ብቻ ነው፡፡

ኢሕአዴግ አስፈላጊውን እርምት ማድረጉ ለሰላምም ለዕድገትም የግድ ጠቃሚ በመሆኑ፣ ሥልጣን የያዘው ኃይል ይህንን ወሳኝና ድፍረት የተሞላው ዕርምጃ ለመውሰድ ብቃቱን ማሳየት ይጠበቅበታል፡፡

ሌላው እጅግ አሳሳቢ የሆነውና ሕገ መንግሥታዊ ግድፈት ነው ብዬ የማምነው ክልሎች ተጠሪነታቸው ለራሳቸው መሆኑ ነው፡፡ እነዚህ ክልላዊ መንግሥታት የይስሙላ ሥልጣን ይዘው ለሕዝባቸው ተገቢውን አገልግሎት እየሰጡ ባለመሆናቸው፣ ሁሉም ክልሎች የግድ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ወይም ለማዕከላዊ መንግሥት ተጠሪና ተጠያቂ መሆናቸው የግድ አስፈላጊ በመሆኑ፣ ይህ የሕገ መንግሥት አንቀጽ በአስቸኳይ መታረም አለበት፡፡

እዚህ ላይ ሶማሌላንድን ምሳሌ ማድረግ ይቻላል፡፡ ይህች አገር የራስዋን ነፃነት ያወጀች ቢሆንም በማንም ዓለም አቀፋዊ ተቋም ወይም መንግሥት ዕውቅና ባለማግኘቷ፣ አንድም ዓይነት የኢንቨስትመንት ወይም የውጭ ብድር ዕርዳታ አግኝታ አታውቅም፡፡ የክልል መንግሥታት ራሳቸውን ማስተዳደራቸው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ተጠሪነታቸው የግድ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ መሆኑ ጠቀሜታው በዋናነት ለክልሎች ነው፡፡ ፍትሐዊና ተመጣጣኝ ዕድገት በመላው አገሪቱ ለማየት፣ እንዲሁም በክልሎችና በፌዴራል መንግሥት መካከል ጊዜ ሳይባክን ውሳኔ ለማስተላለፍ የሕዝብን እርካታ ለማምጣት ወሳኝ በመሆኑ በአፋጣኝ ሊተገበር የሚገባው ተግባር ነው፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ኢዮጵያዊነት ቦሌ ኤርፖርትና ኦሎምፒክ መድረክ ላይ ብቻ እንጂ፣ ከቦሌ ኤርፖርት ወጥተን ወደ ቤታችን ስንሄድ ሁላችንም መንደርተኞች ነን፡፡ ምክንያቱም ኢትዮጵያዊ የሚለው ፓስፖርት የምንገለገልበት ቦሌ ኤርፖርት ብቻ በመሆኑ ነው፡፡

እዚህ ላይ አንድ ገና ዕድሜው በሃያዎቹ ገደማ ያለ ወጣት የነገረኝን ላውጋችሁ፡፡ ወጣቱ የተወለደው በሐዋሳ ከተማ ነው፡፡ እናቱ የካፋ ብሔረሰብ አባል ስትሆን አባቱ ደግሞ የሲዳማ ብሔር አባል ነው፡፡ ይህ ልጅ ከልጅነቱ ጀምሮ የእናቱንና የአባቱን ቋንቋ ሳይሆን አማርኛ እየተናገረ ያደገ በመሆኑ ዕድሜው መታወቂያ ለማውጣት ሲደርስ ወደ ቀበሌ ጽሕፈት ቤት ሄዶ መታወቂያ ያወጣል፡፡ በዚህን ጊዜ ብሔርህ ምንድነው ብለው ሲጠይቁት ‘እናቴ ካፋ ነች፣ አባቴ ደግሞ ሲዳማ ነው፡፡ እኔ የምናገረው አማርኛ ብቻ ነው’ ብሎ ሲናገር መታወቂያ የሚሰጠው ግለሰብ ‘እንግዲያው አንተ አማራ ነህ’ ብሎ መታወቂያው ላይ ሞልቶ ይሰጠዋል፡፡

ልጁም ለነገሩ ብዙም ዋጋ ሳይሰጥ መታወቂያውን ተቀብሎ ሲገለገልበት ይቆይና አንድ ቀን የሐዋሳ ማዘጋጃ ቤት የሥራ ማስታወቂያ አውጥቶ ወጣቶችን ሲቀጥር፣ ይህ ልጅም እንደ ማንኛውም ወጣት ማመልከቻ ሞልቶ ሲወዳደር ፎርሙን የተቀበለው ሠራተኛ ‘አንተ ብሔርህ አማራ ስለሆነ አማራ ክልል ሄደህ ተቀጠር፡፡’ ይህ የሥራ ዕድል የሚፈቀደው ለክልሉ ተወላጆች ነው ሲለው፣ እኔ እዚህ ነው የተወለድኩት ብሎ ለመከራከር ቢሞክርም ሰሚ ባለማግኘቱ ተስፋ ቆርጦ አሁን አዲስ አበባ መጥቶ የታክሲ ሾፌር ሆኖ ለመሥራት እንደተገደደ አጫውቶኛል፡፡

እንግዲህ በእንዲህ ዓይነት አስገራሚ ሁኔታ ዜጐችን በገዛ አገራቸው ወይም በዜግነታቸው ሊያገኙት የሚገባን መብት መከልከል የመጨረሻው ውጤት ምን ሊሆን ይችላል? እኔ በግሌ ይህ ሁኔታ በእጅጉ ያሳስበኛል፡፡ ማንም አገሩን የሚወድ ዜጋም የእኔን ሐሳብ የሚጋራ ይመስለኛል፡፡ ምንጊዜም የሚጠቅመን ትልቅነት ብቻና ብቻ ነው፡፡ ትልቅ፣ ጠንካራና አንድ ስንሆን ብቻ ነው ትልቁን የችግር ቋጥኝ ልንፈነቅል የምንችለው፡፡ ልዩነት ይጨፍለቅ የሚል ሐሳብ ባይኖረኝም አንድነት ተገቢውን ትኩረት ይሰጠው የሚል የፀና እምነት የእኔ ብቻ ሳይሆን፣ የሚሊዮኖች በመሆኑ በዚህ መልክ ብንራመድ የተሻለ ይመስለኛል፡፡

እንደ ማጠቃለያ የመረጥኩት ርዕስ 26 አሮጌ ዓመታት ይለፉና 27ኛውን ዓመት እስኪ ሁላችንም በእርግጥ አዲስ ዓመት እንዲሆን ሁላችንም ቃል ኪዳን እንግባ፡፡ በዓለማችን ያሉ ሥልጣኔዎችን ሁሉ የወለደው ሳይንሳዊ የሆነ ሥርዓት ነው፡፡ ይህንን ሳይንሳዊ ሥርዓት ለመፍጠር ደግሞ እጅግ እልህ አስጨራሽ መንገዶችን መጓዝ ግድ ይላል፡፡ በወኔና በዓላማ የታጠቁ አርበኞች ብቻ ናቸው ለሕዝቦች፣ ለአገር፣ ለትውልድ የሚጠቅም ሥርዓት አውርሰው ያለፉት፡፡ ይህ ደግሞ ከማንም በላይ ሥልጣን ላይ ካለው አካል የሚጠበቅ ተግባር ነው፡፡

ማንኛችንም ከእናታችን ማህፀን ስንወጣ የቋንቋ ችሎታ ይዘን የወጣን ሳይሆን ሆድ ነው ይዘን የወጣነው፡፡ ቋንቋ በምንኖርበት አካባቢ የሚለጠፍብን ክስተት ነው፡፡ በመሆኑም ቅድሚያ ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ የተሻለ ሕይወት ሊያኖረን የሚችለውን ጉዳይ በመሆኑ፣ በዚህ መልክ ብናስብ የተሻለ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ የኢሕአዴግ መንግሥት የተለያዩ መብቶችን ላንዱ በማንኪያ ለሌላው በጭልፋ፣ ለሚፈልጋቸው ደግሞ በአካፋ እየሰጠ በሕዝቦች ዘንድ አመፅ ተረግዞ እንዲወለድ ተግቶ መሥራቱን በማቆም፣ በአገሪቱ ሕገ መንግሥት መሠረት የሚወጡ ፖሊሲዎች ሁሉ በተቻለ መጠን ፍትሐዊ መሆናቸውን 100 ጊዜ ማረጋገጥ አለበት፡፡

በዚህ በያዝነው 21ኛ ክፍለ ዘመን ማንኛውም መንግሥት ሕዝብ ማስተዳደር የሚችለው የዜጐችን መብቶች አክብሮ ብቻ በመሆኑ፣ ይህንን ጉዳይ መንግሥት ተገንዝቦ በፖሊሲ አወጣጥና ትግበራ ላይ ሰፊው ያልተማረው ሕዝብ እስኪነግረው ሳይጠብቅ ምሁራንን እያዳመጠና ስህተቶች ቶሎ ቶሎ እየታረሙ መሥራት ምንም አማራጭ የሌለው ተግባር ነው፡፡ በእኔ እምነት ላልተማረ ኅብረተሰብ አመፅ ቋንቋ ነው፡፡ ሰዎች ብሶታቸውን የሚገልጹበት መድረክ ሲያጡ ንብረት በማውደምና ሌሎች አውዳሚ ተግባራትን በመፈጸም መልዕክት ለማስተላለፍ ይሞክራሉ፡፡ እንዲያም ሲል እንደ ቱኒዝያዊው መሐመድ ቡአዚዝ ራሳቸው ላይ ቤንዚን በማርከፍከፍ መልዕክት ለማስተላለፍ ይሞክራሉ፡፡ ይህ ሁሉ የሚሆነው መንግሥት ችግሮችን በራሱ መንገድ ፈልጐ ማግኘትና መፍትሔ ማፈላለግ ሲሳነው ነው፡፡ ሕዝባዊ አመፅ ደግሞ ልክ እንደተሰበረ ግድብ አንዴ ውኃውን መልቀቅ ከጀመረ የሚያቆመው ነገር ባለመኖሩ፣ ከወዲሁ እልህ አስጨራሽ ዕርምጃዎችንና እርምቶችን በመውሰድ ራስንም አገርንም ማዳን ምንም አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው፡፡

አገሪቱ በአሁኑ ጊዜ በደቦ የምትመራ በመሆኑ አዲስ ሐሳብ በኢሕአዴግ ማዕከላዊ ኮሚቴ ውስጥ ማመንጨት ለከፍተኛ አመራሮች አደጋ ያስከትላል የሚል እምነት ቢኖረኝም፣ ውሳኔውን አለማስተላለፉ ከዚያ የከፋ ችግር ስላለው እዚህ ላይ ወገብን ጠበቅ ማድረጉ የግድ ይላል፡፡ አራቱ አንጋፋ ከፍተኛ የኢሕአዴግ ባለሥልጣናት በቅርቡ በቴሌቪዥን መስኮታችን ብቅ ብለው አሁንም ሕገ መንግሥቱ ምንም እንከን እንደሌለውና አፈጻጸሙ ላይ ብቻ ችግር እንዳለ ነግረውን ነበር፡፡ ይህ ግን ጭልጥ ያለ ግትርነትና ኃላፊነት የጐደለው አመለካከት በመሆኑ፣ አሁንም በድጋሚ በጥልቅ አስቡበት እያልኩ 2009 ዓ.ም. ጨምሮ 26 ዓመታት አሮጌ ብለን እንውሰዳቸውና በ2009 ዓ.ም. ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጀምሮ እስከ ዝቅተኛው የኅብረተሰብ ክፍል ያለን ዜጐች ሁላችንም ለሰላምና ለእርምት ዝግጁ ሆነን ከሠራን፣ እውነተኛ መልካም አዲስ ዓመት የምናይበት ጊዜ በቅርብ ርቀት ነው ብዬ አምናለሁ፡፡  

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

           

Standard (Image)

የኤርትራ የወቅቱ ሁኔታና የኢትዮጵያ ዕጣ

$
0
0

  በበሊሕ ላማ

 
በአሮጌው ዓመት እዚህ አገር ላይ ከደረሰ የፀጥታ ችግር ጀርባ ሕግዴፍ-ሻዕቢያ አለበት ያልተባለበት አጋጣሚ ቢኖር ከጋምቤላ ሕፃናት በታፈኑና ከብቶች በተዘረፉ ወቅት ብቻ ነው፡፡ ከዚያ ውጪ አርባ ምንጭም፣ አሩሲም፣ ጎንደርም፣ ምዕራብ ሸዋም… ብቻ በየትኛውም አቅጣጫ ከነበሩ የዘንድሮ ፖለቲካዊ ቀውሶች ዙሪያ የአስመራው መንግሥት እጁን በረጅሙ ስለማስገባቱ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ደጋግመው ተናግረዋል፡፡ እርግጥ ነው የኤርትራ መንግሥት የተለያየ ግብና ህልም ላላቸው ኢትዮጵያውያን የፖለቲካ ኃይሎች በአደባባይ ድጋፍ ያደርጋል፡፡ ተደጋፊዎቹም ይህንን አስተባብለው አያውቁም፡፡ ይልቁንም እየተደረገላቸው ያለውን ድጋፍም በአደባባይ ሲያወሩ ተደምጠዋል፡፡ እነዚሁ ቡድኖችም ሆኑ ራሱ ሻዕቢያ ደግሞ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ምኞታቸውን ለማሳካት መጣደፋቸው አይቀርም፡፡ ፀረ ኢሕአዴግ አቋማቸው ብቻ አንድ የሚያደርጋቸው ከአምስት በላይ ቡድኖች ኤርትራ የተቀመጡት በአስመራ መንደሮች ውስጥ ጋራዥ ለመክፈት አይደለም፡፡ አንድ ቀን ጠብ የሚል ነገር ቢኖር ብለው ነው፡፡ እናም የትኛውንም አጋጣሚ መጠቀማቸው የማይቀር ነው፡፡

እኛ የዚች አገር ዜጎች ግን አንድ ወፍራም ጥያቄ ማንሳት ይገባናል፡፡ ያቺ ትንሽ አገር፣ ዝቅተኛ የጦር አቅምና የሕዝብ ቁጥር ይዛ ይህንን ግዙፍ መንግሥትና አገር እንዴት እንዲህ ልታሸብር ቻለች? አርባጉጉ ላይ ለሚፈጠር ግጭት፣ ጎንደር ላይ ለሚኖር አመፅ፣ ምዕራብ ሸዋ ላይ ለሚተኮስ ጥይት በሙሉ ተጠያቂው ሻዕቢያ ከሆነ እኛም መንግሥታችንን እንዲህ ስንል መጠየቅ አለብን፡፡ ‹‹በአራቱም ማዕዘናት ለመግባት የሚያስችለውን ቀዳዳ ባትከፍትለት ኖሮ፣ ጠንካራ የፀጥታ ጥበቃ ቢኖርህ ኖሮ፣… ሻዕቢያ ዕድሉን ታገኝ ነበርን? ከሰሜን እስከ ደቡብ የተነሱ ጥያቄዎች በሙሉ ጀርባቸው ሻዕቢያ ነው ከተባለ፣ ሻዕቢያ ከአስመራ ተነስታ ጎንደርንም አልፋ፣ ወለጋንም ተሻግራ…አምቦ እስከምትደርስ ድረስ አንተ የማንን ጎፈሬ ታበጥር ነበር? ይህስ ማንቀላፋትህ የአገር ሀብት የሆነውን የደኅንነት ተቋማችንንና መከላከያችንን እንዳናምነው አያደርገንም ይሆን?›› ማለት ቢኖርብን ነው፡፡

የእኛ መንግሥት ሁሌ ‹በጎቼን ቀበሮ በላብኝ› እያለ ጎረቤቶቹን ሲያታልል ኖሮ መጨረሻ ላይ የእውነት ሲበሉበት ረዳት እንዳጣው ውሸታም እረኛ እንዳይሆን ያሰጋል፡፡ ከጎንደር እስከ አርባ ምንጭ፣ ከኮንሶ እስከ አምቦ… ሁሌም ሻዕቢያ አፈነ፣ ተኮሰ፣ ገደለ፣ አሸበረ… እያለ የሚዘፍናትን ሙዚቃ (ሙዚቃዋ እውነትነት ቢኖራትም ቅሉ) ሕዝብም ሰልችቶ ነገርየውን የሁለት አገር ጉዳይ ሳይሆን፣ የሁለት መንግሥታት ቀጣናዊና ታሪካዊ ቁርሾ እንዲሁም አብሮ አደጋዊ መናናቅ አድርጎ የሚቆጥር ማኅበረሰብ መብዛቱ አይቀርም፡፡

ሌላኛዋ የተሰለቸች ነጠላ ዜማ ‹ተመጣጣኝ ዕርምጃ እንወስዳለን› የምትለዋ ነች፡፡ ‘ተመጣጣኝ’ ሲባል ምን ማለት ነው? የእነሱ ዓላማ የአዲስ አበባው መንግሥት እንዲወገድ እስከ ቀራኒዮ የሚደርስ ጥረት ማድረግ ነው፡፡ ታዲያ የኢትዮጵያ ‘ተመጣጣኝ’ ዓላማ የአስመራውን ሥርዓት እስከመቀየር ይደርሳልን? ወይስ ፆረናን አያልፍም? ወይስ ሁለት ጥይት ሲተኩሱ ሁለት መተኮስ? 50 ኢትዮጵያውያንን አፍነው ሲወስዱ 50 ኤርትራውያንን ጠልፎ ማምጣት? ይህንን እንኳ ያብራራ ባለሥልጣን እስካሁን የለንም፡፡

የሆነ ሆኖ ይቺን ከአሥር ዓመት በላይ የተጠቀማትን ፋሽን ወደመጣችበት መልሶ አዲስና ገቢራዊ ሥልት መጠቀም ይገባዋል፡፡ የመጀመሪያውና ዋነኛው መላ ለአገራዊ ቀውሶች ፈጣንና የሠለጠነ ምላሽ መስጠት ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ በቀጥታ በኤርትራ ላይ የሚተገበር ሥራ ሊሆን ይገባዋል፡፡ ይህ አዲስ ዘዴ ኤርትራን መውረር ላይሆን ይችላል፡፡ ለሁሉም ቀውስ ሻዕቢያን ከመክሰስም በላይ፣ ከተመጣጣኝ ዕርምጃም በላይ መሆን ግን አለበት፡፡ እንዲህ ያለው ጉዳይ ከወዲሁ ካልታሰበ የነገዋ ኤርትራ አስፈሪ ነች፡፡

የወደፊቷ ኤርትራ

ኤርትራ በምዕራቡ ዓለምም ሆነ በዓረቡ ወገን ከኢትዮጵያ በበለጠ ተመራጭ ነች፡፡ ምክንያቱም ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊና ምጣኔ ሀብታዊ ስትራቴጂክነትን የታደለች አገር ናት፡፡ ይህ ደግሞ ዝም ተብሎ የሚወራ ሳይሆን የሚታይ ነው፡፡ ከዓለማችንን ነዳጅና ሸቀጥ ውስጥ 70 በመቶ የሚሆነው የሚጓጓዘው በቀይ ባሕር ነው፡፡ ይህ ባሕር በቀጥታ ከስዊዝ ቦይ ጋር ይገናኛል፡፡ ይህ ቦይ ደግሞ ምዕራቡን ዓለም ከእስያ ጋር የሚያገናኝ ትልቅ የንግድ መሥመር ብቻ ሳይሆን በሜድትራኒያን ባሕርና በዓረብ ባሕረ-ሰላጤ ያለውን የአሜሪካ ባሕር ኃይል የሚያገናኝ ነው፡፡ ቦዩ ተጠሪነቱ ለግብፅ ነው (ኤርትራንና ግብፅን አንድ የሚያደርጋቸው ዋነኛ አጀንዳ ደግሞ አለ፡፡ ከኢትዮጵያ ጥቅም በተቃራኒ የቆመው ፍላጎታቸው)፡፡ ቀይ ባሕር ደግሞ ኤርትራን በብዙ ኪሎ ሜትሮች የሚያዋስን ነው፡፡ ባሕሩ የደኅንነትና የወታደራዊ አጀንዳዎች ማንፀሪያም ነው፡፡ ይህንን ባሕር ለመቆጣጠር ሲባል ኤርትራን የማይፈልጋት የለም፡፡ ከአሜሪካ እስከ ኢራን፣ ከአውሮፓ ኅብረት እስከ ዓረብ ሊግ … ከኤርትራ ጋር መወዳጀት ይፈልጋሉ፡፡

ለዚህ እማኝ ይሆነን ዘንድ በቅርቡ የመንግሥታቱ ድርጅት ያወጣውን ሪፖርት መመልከት ይበቃል፡፡ የድርጅቱ የሶማሊያና የኤርትራ ታዛቢ ቡድን ባሳለፍነው ዓመት ሁለተኛ አጋማሽ ላይ (2008 ዓ.ም.) ይፋ ባደረገው ሰነድ፣ የኢሳያስ መንግሥት ለአልሸባብ ድጋፍ ስለማድረጉ የሚያሳይ ማስረጃ አላገኘሁም ብሏል፡፡

በዚያው ሰሞን ይኼው ታዛቢ ቡድን ያወጣው ሌላ ዘገባ ደግሞ፣ የአስመራ ባለሥልጣናት በሰብዓዊ መብት ጥሰት ላይ ስለተሰማሩ በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት እንዲከሰሱ የሚያሳስብ ነበር፡፡ ሆኖም የቡድኑ ምክረ ሐሳብ ይተገበር የነበረው የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባላት ሲያፀድቁት ነበርና ወደ ምክር ቤቱ ያመራው ይኼ ጉዳይ፣ በቻይናና በአሜሪካ ውሳኔ (ድምፅን በድምፅ የመሻር ሥልጣን) ውድቅ ተደርጓል፡፡

ከላይ ያሉትን ሁለት ነጥቦች በተን አድርጎ ማየት ያሻል፡፡ ቡድኑ ‹‹ኤርትራ  አልሸባብን ስትደግፍ የሚያሳይ ማስረጃ አላገኘሁም›› ማለቱ ለአስመራ እፎይታ ነው፡፡ ይህ ቀነ ገደብ ያልተቀመጠለት ማዕቀብ ሊነሳ የሚችልበት ዕድል እንዳለ የሚጠቁም ነው (ኤርትራ ላይ ማዕቀብ የተጣለው ለአልሸባብ ድጋፍ ታደርጋለች በሚል መሆኑን ልብ ይሏል)፡፡ በአንድ በኩል የሶማሊያው ጽንፈኛ ቡድን እየተሸነፈ መሄድ እነ ኢሳያስ አፈወርቂ ሳይወዱ በግድ ያደርጉታል ተብለው የተከሰሱበትን ድጋፍ እንዲያቋርጡ ሊገደዱ ይችላሉ፡፡ በሌላ ወገን ከኤርትራ ጋር መወዳጀት የሚሻ ሁሉ የነ ኢሳያስን ለአልሸባብ ድጋፍ አለማድረግ በማሳያነት በመጥቀስ  ማዕቀቡ እንዲነሳ ሊወተውት ይችላል፡፡

ሁለተኛው ነጥብ  አሜሪካና ቻይና ለምን የታዛቢ ቡድኑን ምክረ ሐሳብ ውድቅ አደረጉት የሚለው ነው፡፡ እነዚህ አገሮች በአፍሪቃ ቀንድ ግልጽ ፍላጎት አላቸው፡፡ ዋሽንግተን የቀጣናው የፖለቲካ ካራ ከእጇ እንዳይወጣ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ ከ1,300 ኪሎ ሜትር በላይ የባሕር ድንበር ያላትን ኤርትራን መምረጧ የማይቀር ነው፡፡ ቻይናም በቀላሉ መግባትና መውጣት የሚያስችሉ ወደቦች ያሏትን ኤርትራን ለንግድና ለኢንቨስትመንት አብዝታ ትሻታለች፡፡ ለዚህ ደግሞ ማዕቀብ የተባለ እንቅፋት እንዲያጥራት አትፈልግም፡፡ ቤጂንግ በዓለም የደኅንነትና የሰላም ጉዳይ ላይ መሪ ለመሆን ከአሜሪካ ጋር ለገባችበት ትንቅንቅ፣ ተፈጥሯዊ ስትራቴጂክነት ያላትን ኤርትራን መሣሪያ ማድረግ አትጠላም፡፡ እናም የኤርትራን ማዕቀብ አላስፈላጊነት ሁለቱ አገሮች ከተስማሙበት ነገሩ ሁሉ ያልቅለታል፡፡ ከላይ የተጠቀሰውን የሁለቱን አገሮች ውሳኔ ለማዕቀቡ መነሳት ምልክት አድርጎ መውሰድ ይቻላል፡፡

እነዚህ አገሮች የኤርትራን ሁናቴ ከሰብዓዊ መብት አያያዝና ከዴሞክራሲያዊነት አንፃር መዝነው ማዕቀቡ እንዳይነሳ ያደርጋሉ ማለት ዘበት ነው፡፡ በአንድ በኩል አሜሪካ ጥቅሟ እስከተከበረ ድረስ (የፖለቲካዊና የወታደራዊ ስትራቴጂክነት ጥቅሟ) ለአገሮች የሰብዓዊ መብት አያያዝ፣ ሕገ መንግሥታዊነት፣ ወዘተ የሚባሉ ጽንሰ ሐሳቦችን እንደ ቅድመ ሁኔታ አታስቀምጥም፡፡ ለዚህ እንደ ሳዑዲ ዓረቢያ ያሉ ወዳጆቿን መጥቀስ ይቻላል፡፡ በዓለማችን ሰብዓዊ መብቴችን በመጣስ አንደኛ አገር የንጉሣውያኑ ምድር ሳዑዲ ግንባር ቀደም የአሜሪካ አጋር ነች፡፡ ቻይና ደግሞ በአገሮች የውስጥ ጉዳይ ላይ ጣልቃ የማይገባ የውጭ ጉዳይ መርሆ ያላት በመሆኗ፣ የኤርትራን ወዳጅነት ያለቅድመ መመዘኛ እንድትቀበለው ያደርጋታል፡፡

ማዕቀቡ ሊነሳ የሚችልበት ሌላም ፍንጭ አለ፡፡ የኤርትራ መንግሥት የየመን ሁቱዎችን ለመደምሰስ በሳዑዲ ዓረቢያ እየተመራ የመን የገባውን ቡድን ተቀላቅሏል (በእርግጥ ኤርትራውያን ያስተባብላሉ)፡፡ የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ግን የሻዕቢያ መንግሥት ከሁለት ሺህ በላይ እግረኛ ሠራዊት ወደ የመን መላኩን ደጋግመው ዘግበውታል፡፡ ከዚያም ባሻገር የአሰብ ወደብን ዓረቦቹ ዘለግ ላሉ ዓመታት በሊዝ መያዛቸው፣ ሳዑዲ መራሹ ቡድን ለፀረ ሁቱ ዘመቻ የሚያሠለጥንበትን ቤዝ ከኤደን ወደ ኤርትራ ማሻገሩ፣ ኤርትራ ከነ ሳዑዲ የገንዘብ፣ የጦር መሣሪያና የነዳጅ ድጎማ እያገኘች መሆኗ (ሳዑዲ የጦር መሣሪያውን የምታገኘው ከአሜሪካና ከብሪታኒያ መሆኑ ይሰመርበት)፣ አደባባይ ላይ የዋለ እውነት ነው፡፡ ይህ ሁሉ ሲደረግ (በሌላ ቋንቋ ማዕቀቡ ሲጣስ) ማዕቀቡን የጣሉት እነ አሜሪካም ሆኑ የመንግሥታቱ ድርጅት አይተው እንዳላየ መሆናቸው፣ ማዕቀቡ ከኤርትራ አናት ላይ ገለል ሊል የሚችልበት ዋዜማ ላይ እንደደረሰ የሚጠቁም ነው፡፡

ባሳለፍነው ክረምት የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ለደቡብ ሱዳን ተጎጂዎች የሚያስፈልገውን አንድ ሺሕ ሜትሪክ ቶን የዕርዳታ እህል ያጓጓዘው በምፅዋ ወደብ ላይ ነው፡፡ ይህ እ.ኤ.አ ከ2006 ወዲህ የመጀመሪያ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ ኤርትራ ለቀጣናው የሰብዓዊ መብት ግልጋሎቶች ወደቦቿን ክፍት አደረገች ማለት ዓለም አቀፍ ወዳጆቿን (ከመንግሥታትም ሆነ ከረድኤት ተቋማት ጋር) ለማብዛት እየተንደረደረች ነው ማለት ነው፡፡ እነሱም በዚህ ደረጃ ጠቀሜታዋን ከተረዱት የኤርትራ ማዕቀብ እንዲነሳ ጫና ማድረጋቸው አይቀርም፡፡ (እነ አሜሪካ እንኳን የኤርትራን ማዕቀብ የኩባንና የኢራንንም አንስተዋል)፡፡ ስለዚህ የወደፊቷ ኤርትራ ማዕቀብ የተነሳላትና በጉልበተኞቹ አገሮች የምትመረጥ የመሆን ዕድል ያላት ነች፡፡

ኤርትራና የአውሮፓ ኅብረት

በእርግጥ የአሜሪካ መንግሥትና የአውሮፓ ኅብረት በውሳኔ ተለያይተውም፣ ተራርቀውም አያውቁም፡፡ እናም ኅብረቱ በኤርትራ ላይ ከአሜሪካ የተለየ አመለካከትና ፖሊሲ ይኖረዋል ተብሎ አይጠበቅም፡፡ ይልቁንም በተግባራዊነት የብራሰልሱ ድርጅት ከአሜሪካም የቀደመ ሥራ ሠርቷል፡፡

የኤርትራ መንግሥት ባሳለፍነው ጳጉሜን 3 ቀን 2008 ዓ.ም. 18.7 ሚሊዮን ዩሮ ከአውርፓ ኅብረት አግኝቷል፡፡ ይህ ገንዘብ በኤርትራ ስድስት ቦታዎች ላይ የጠብታ መስኖን ለማልማት የሚውል ነው፡፡ ይህንን ሥራ ለማከናወን ደግሞ በዘርፉ የሚያስመሰግን ልምድ ያላቸው የእስራኤል ኩባንያዎች ውል ተፈራርመዋል፡፡ ‹‹የኤርትራን ግብርናና የምግብ ዋስትና ለማገዝ›› በሚል መርሐ ግብር ከኅብረቱ የተለቀቀው ይኼ ገንዘብ ብራሰልስና አስመራ እየተናበቡ ስለመሆኑ አስረጂ ነው፡፡ በኅብረቱ የኤርትራ ጉዳዮች ኃላፊ ፔሬ ፊሊፔ እንደተናገሩት እ.ኤ.አ. ከ2013 አንስቶ የኤርትራን አርሶ አደሮች ምርታማነት ለመጨመር ለአገሪቱ መንግሥት የአውሮፓ ኅብረት ድጋፍ ሲያደርግ ከርሟል፡፡ የዚህ አዝማሚያ የሁለቱን ወገኖች የወደፊት ግንኙነት የሚጠቁም ነው፡፡ ኅብረቱ ያደረገው የንዘብ ድጋፍም ከዚሁ የሚመነጭ ነው፡፡

በአገሪቱ ሁለተኛ ሰው በአቶ የማነ ገብረአብ (የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የፖለቲካ አማካሪ) የተመራ የልዑካን ቡድን በመስከረም ወር መግቢያ ላይ ወደ ጀርመን  አቅንቶ ነበር፡፡ ይህ የሆነው ኅብረቱ ሚሊዮን ዩሮዎችን ለአስመራው መንግሥት ከሰጠ በኋላ ነው፡፡ ወደ በርሊን የመሄዳቸው ምክንያትም በአውሮፓ ኅብረት ውስጥ የአውራነት ሚና ካለው የጀርመን መንግሥት ጋር ለመወያየት ነበር፡፡ በዚህም ከጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ከኢኮኖሚ ሚኒስቴር ጋር ተገናኝተዋል፡፡ የጀርመን ቆይታቸውም በመግባባት ላይ የተመሠረተና ለወደፊት ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን በጋራ ለመከወን በመስማማት የተጠናቀቀ መሆኑን አቶ የማነ ለጀርመን መገናኛ ብዙኃን በሰጡት ቃለ መጠይቅ ተናግረዋል፡፡ ጀርመን ኤርትራን በቅን ልቡና ተቀበለቻት ማለት 27ቱም የአውሮፓ ኅብረት አባል አገሮች ተቀበሏት ማለት መሆኑን መጠርጠር ያስፈልጋል (የአንገላ መርከል አስተዳደር በኅብረቱ ውስጥ ያለውን ጉልበት ልብ ይሏል)፡፡ ስለዚህ ኅብረቱም የኤርትራ ማዕቀብ እንዲነሳ መፈለጉ አይቀርም፡፡ የዚህ ፍላጎት ምክንያት ሁለት ነው፡፡ አንደኛው ከላይ እንደተገለጸው የአውሮፓ ኅብረትም የኤርትራን ስትራቴጅካዊነት ይፈልገዋል የሚለው ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ የኤርትራ ስደተኞች ናቸው፡፡ ለኅብረቱ አባል አገሮች የስደተኞች ነገር ራስ ምታት መሆን ከጀመረ ቆየ፡፡ በዓለም ላይ ብዙ ዜጎቻቸው ወደ አውሮፓ ይሻገራሉ ከሚባሉ አገሮች ውስጥ ኤርትራ ከመጀመሪያዎቹ ተርታ ትጠቀሳለች፡፡ እናም ኅብረቱ ከኤርትራ ባለሥልጣናት ጋር ተቀራርቦ በመሥራት ይህንን ራስ ምታቱን ማስታገስ ይፈልጋል፡፡ በአጭር አገላለጽ የኤርትራ ስደተኞችን ቁጥር ለማቃለል ከአስመራው መንግሥት ጋር መቀራረብ ለኅብረቱ ወሳኝ ነው፡፡

ኤርትራና የዓረብ ሊግ

ኢሳያስ አፈወርቂ ገና ከትጥቅ ትግሉ ዘመን ጀምሮ ከዓረቡ ዓለም ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዳላቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ወዲ አፎም ምንም እንኳ የኦርቶዶክስ ክርስትና አማኝ ቢሆኑም ጀለቢያ ሳይቀር እየለበሱ መስጂድ ገብተው ከዓረብ ጎበዛዝት ጋር ይዶልቱ እንደነበር ድርሳነ ሳሕላቸው ይተርካል፡፡

ይህንን ጉዳይ በአገር መሪነታቸው ዘመን ጠንከር አድርገውት ቀጥለዋል፡፡ ኤርትራንም የዓረብ ሊግ ታዛቢ አባል አድርገዋታል፡፡ ላለፉት 20 ወራት በየመን የሚካሄደውን ጦርነት ከነሳዑዲ ዓረቢያ ጋር ሆነው መቀላቀላቸውም ለዚሁ ለዓረቡ ዓለም ያላቸውን ታማኝነት የሚያሳይ ነው፡፡ ባለፉት አሥር ዓመታት አስመራ ከምዕራቡ ዓለም ያጣችውን ድጋፍ ለማካካስ ከዓረቡ ዓለም ጋር የሙጥኝ ማለቷ የጠራራ ፀሐይ ሀቅ ነው፡፡ አቶ ኢሳያስ በተደጋጋሚ የዓረብ ሊግ አባል አገሮችን መጎብኘታቸው (ወደ ሱዳን ካርቱም፣ ወደ ግብፅ ካይሮ፣ ወደ ሳውዲ ሪያድ፣ ወደ ኳታር ወዘተ መመላለሳቸው) ከእነዚሁ የሰሜን አፍሪቃና የመካከለኛው ምሥራቅ ወዳጆቻቸው ጋር ያላቸውን ሽርክና ለማጠናከር አልመው ለመሆኑ ዕሙን ነው፡፡ እነዚህ አገሮችም ለኤርትራ ነዳጅ፣ ገንዘብና የጦር መሣሪያ ከመደጎምና ከማበደር አልፈው ወደብ በሊዝ እስከመከራየት ደርሰዋል፡፡ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች የአሰብ ወደብን ለሰላሳ ዓመት በሊዝ ተከራይታዋለች፡፡ በዳህላክ ደሴት ላይ ሰፍሮ የነበረው የኢራን ጦርም እነ ኢሳያስ የሺዓውንም የሱኒውንም አገር አሟጦ ለመጠቀም እያደረጉ ያሉትን መውተርተር ያመለክታል፡፡ በእርግጥ ኢራኖች በየመን ጦርነት ከተቀሰቀሰ በኋላና ከሳዑዲ ጋር የውክልና ጦርነት ውስጥ ተፋፍመው ከገቡ ወዲህ (ሁቱዎች በኢራን የሚደገፉ ሺዓዎች ናቸው) ዳህላክ ደሴትን ትተው ወጥተዋል፡፡ እሥራኤል ዛሬም ምፅዋ ላይ አለች፡፡

ይህን ኤርትራ በዲፕሎማሲ ያመጣችው ሳይሆን ተፈጥሯዊ ስትራቴጅክነቷን ተጠቅማ ያገኘችው ዕድል ነው፡፡ ከኤርትራ የተሻለ ጥቅም እንደሚያገኙ በሚገባ የተገለጠላቸው እንደ ኳታር ያሉ አገሮችም ኤርትራን ከጠላቶቿ ለማስታረቅ ጥረት ሲያደርጉ እየታዩ ነው፡፡ ባሳለፍነው ዓመት የመጨረሻ ወራት በኳታር አደራዳሪነት ኤርትራ የጅቡቲ እስረኞችን ፈትታ ሰጥታለች፡፡ ይህ የኳታር ጥረት ተጠናክሮ ከቀጠለ ሁለቱን አገሮች ወደ ወዳጅነት ማምጣቱ አይቀርም፡፡ የኳታር መንግሥት ይህንን ሁሉ የሚያደርገው ኢትዮጵያን ብቻዋን ለማስቀረት በማሰብ መሆኑን መጠርጠር ያስፈልጋል (ኢትዮጵያና ኳታር ሄድ መጣ የሚል የዲፕሎማሲ ግንኙነት እንዳላቸው ይታወቃል)፡፡ በየመን እየተካሄደ ያለው ጦርነት በሁቱ አማፅያን ሽንፈትና በነ ሳዑዲ ዓረቢያ የበላይነት የሚጠናቀቅ ከሆነ (አዝማሚያው እንደዚያ ይመስላል) ለኤርትራ ፍሰሐ ነው፡፡ ምክንያቱም የኢሳያስ መንግሥት  የወታደሮቹን ደም እየገበረ ያለው እሱ የሚፈልገው ቡድን ወደ ሥልጣን እንደሚመጣ ስለሚያውቅ ነው፡፡ ይህ ለኢትዮጵያ ሥጋት መሆኑ አይቀርም፡፡ የወደፊቷ የመን ከአዲስ አበባ ይልቅ ጎረቤቷን አስመራን ልትመርጥ ትችላለች፡፡

የኢትዮጵያ አማራጮች

አፍሪቃዊቷ ሰሜን ኮሪያ የሚል መጠሪያ የተሰጣት ኤርትራ ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የነበራት መገለል ከተቋጨ የምሥራቅ አፍሪቃ የኃይል ሚዛን ይቀያየራል፡፡ ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች የአስመራው መንግሥት ውጫዊ ትኩረት ካገኘ፣ በኢትዮጵያ ላይ ለሚያስበው እኩይ ድርጊት መልካም ፖለቲካዊ ታኮ (political buttress) እንደሚሆንለት ዕሙን ነው፡፡ ኃያላኑ አገሮችም ቢሆኑ ጥቅማቸው እስከተጠበቀ ድረስ ሌላው ቀርቶ ኢትዮጵያን ለመውረር ቢነሳ ሃይ አይሉትም፡፡ ይህ ደግሞ ሳዑዲ ዓረቢያ በየመን ወረራ ስትፈጽም እነ አሜሪካ ድጋፍ ሲያደርጉ እየተስተዋለ ያለ ተሞክሮ ነው፡፡

ከዚህም ባሻገር ኤርትራ በኢትዮጵያ ላይ ላዘመተችው የውክልና ጦርነት (proxy war) በቂ የፋይናንስና ዓለም አቀፋዊ ይሁንታ ልታገኝ ትችላለች፡፡ በኢሕአዴግ ላይ የሚነሳው ተቃውሞ አገራዊ መልክ ይዞ ቢቀጥልና ግንባሩ በኃይል የመገርሰስ ዕድል ቢገጥመው እነ አሜሪካ ሁለተኛ አማራጭ (plan B) ማሰባቸውና ማቀዳቸው አይቀርም፡፡ ይህንን አማራጭ ሊያገኙ የሚችሉት ደግሞ አስመራ ላይ ከተጠራቀሙት ቡድኖች መካከል መሆኑ የማይቀር ነው፡፡ ስለዚህ ኤርትራ ለምታዘምታቸው ፀረ ኢትዮጵያ ‹አርበኞች› ሳይታሰብ የኃያላኑን ድጋፍ የምታገኝበት አጋጣሚ ይኖራል፡፡

ይህ ሁሉ ከመሆኑ በፊት ኢትዮጵያ አማራጮቿን አሟጥጣ መጠቀም ይገባታል፡፡ እነዚህ አማራጮች ምንድን ናቸው የሚለው ጉዳይ ዓብይ ነጥብ ነው፡፡ መቼም ሰላማዊ ድርድር የሚባለው የ21ኛው ክፍለ ዘመን ቁጥር አንድ የፖለቲካ ዘዴ (political technique) አስመራ ላይ ሻዕቢያ፣ አዲስ አበባ ላይ ኢሕአዴግ እስካሉ ድረስ የማይታሰብ ነው፡፡ ሁለቱ ድርጅቶች ግልጽ መናናቅና መጠላላት ተጠናውቷቸዋል፡፡ በዚህ ሁኔታ ለጠረጴዛ የሚበቃና የሚቀራረብ ሐሳብ ይኖራቸዋል ተብሎ አይገመትም፡፡ እናም ይኼኛው አማራጭ ለጊዜው ገቢራዊ ሊሆን የሚችልበት ዕድል ከመርፌ ቀዳዳም የጠበበ ነው፡፡

ፕሮፌሰር አሌክስ ዲ ዎል ከሳምንታት በፊት ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ከማዕቀቡ በኋላ ስላለችው ኤርትራ ኢትዮጵያ ያስቀመጠችው አማራጭ የለም፡፡ ይህ የአገሪቱ መንግሥት ጉዳዩን አርቆ እንዳላየው የሚያመለክት ነው፡፡ ስለዚህ አሁንም ቢሆን የኤርትራ ማዕቀብ እንዲራዘም ለማድረግ የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ መንግሥት ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ሥራ ይጠብቀዋል፡፡ ኤርትራ ከዓረቡ ዓለም ጋር እያደረገች ያለችው ሽርጉድ (ከላይ በዝርዝር እንደተመለከተው) የተጣለባትን ማዕቀብ የሚጥስ መሆኑን የሚያስገነዝብ የሕዝብ ግንኙነት ሥራ በዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ዘንድ መሥራትና ማሳመን ይገባዋል፡፡ የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ መንግሥት እስካሁን አልሸባብን በይፋ አለማውገዙም፣ ኢትዮጵያ የኤርትራን ማዕቀብ ለማስቀጠል ለምታደርገው ጥረት እንደ አንድ ማጣቀሻ ሊያገለግላት ይችላል፡፡ ይህንን ሁሉ ለማድረግ ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2017 ወርቃማ ዕድል (golden opportunity) አላት፡፡ ይህ አጋጣሚ የፀጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል የመሆኗ ነገር ነው፡፡

ባሳለፍነው ሐምሌ በኒውዮርክ በተካሄደው የመንግሥታቱ ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ኢትዮጵያ የድርጅቱ ጉልበተኛ ክንፍ በሆነው የፀጥታው ምክር ቤት  ውስጥ እ.ኤ.አ. ከጥር 2017 አንስቶ ባሉት ሁለት ዓመታት እንድትቆይ የሚያስችላትን የ185 አገሮች ድምፅ አግኝታለች፡፡ የዚህ ምክር ቤት አባል መሆን ከሚያስገኛቸው ጥቅሞች አንዱ፣ በምክር ቤቱ ውስጥ የራስን ጉዳይ የመወያያ አጀንዳ አድርጎ ማስያዝ ማስቻሉ ነው፡፡ ስለዚህም ኢትዮጵያ በሚኖራት የምክር ቤቱ ቆይታ የኤርትራን ማዕቀብ የማራዘሙን ጉዳይ ትኩረት ሰጥታ ልትከውነው ይገባል፡፡ አሁን ግን ይህ ዘላቂ መፍትሔ አይደለም፡፡ እናም የአዲስ አበባ ባለሥልጣናት የረጅም ጊዜ ዕቅድ ማስቀመጥና አሁን ካለው ‹ሰላምም ጦርነትም የለም› ከሚለው መርሆ የተሻገረ ገቢራዊ ሐሳብ ሊያስቡ የሚችሉበት ጊዜ የቀረበ ይመስላል፡፡ ይኼ ገቢራዊ ሐሳብ በኤርትራ ያሉ የኢሳያስ መንግሥት ተቃዋሚዎችን (እንደ የቀይ ባሕር አፋሮች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ያሉ ታጣቂ ኃይሎችን) ማጠናከርና አለም አቀፋዊ ድጋፍ እንዲኖራቸው ማገዝ ሊሆን ይችላል፡፡ እነዚህንና ሌሎች መንገዶችን አጢኖ መሄድ የማይችል የኢትዮጵያ መንግሥት ካለ ግን ኤርትራ የተባለች ትንሽ አገር የቀጣናውን ግዙፍ የፖለቲካ መዘውር እጇ ማስገባቷ የማይቀር ነው፡፡ በኢትዮጵያና በሕዝቧ ላይ ክፉ በማሰብ ዕድሜያቸውን የፈጁት አቶ ኢሳያስም ከመቐሌ እስከ ሞያሌ ሊፈነጩ የሚችሉበት አጋጣሚ አይፈጠርም ብሎ መከራከር አይቻልም፡፡

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው yayeshime02@gmail.comማግኘት ይቻላል፡፡ 

 

 

Standard (Image)

‹‹አለባብሰው ቢያርሱ ባረም ይመለሱ››

$
0
0

በጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)

ከሰሞኑ ኢሕአዴግ ‹‹ጥልቅ ተሃድሶ›› ያስፈልገኛል ማለቱን ሰምተናል፡፡ ካለንበት የፖለቲካ ቀውስ ለመውጣት ለውጥ ያስፈልጋል ብለን ለምናምን ሁሉ፣ በሥልጣን ላይ ያለው ፓርቲ ተሃድሶ ያስፈልገኛል ማለቱን በአዎንታዊ መልኩ ልናየው የሚገባ ቢሆንም፣ ‹‹ጥልቅ›› የተባለው ተሃድሶ በአስፈላጊው ደረጃ ‹‹ጥልቅ›› አይሆንም የሚለው ሥጋት ደግሞ ነገሩን ሁሉ በጥርጣሬ እንድናይ ግድ ይለናል፡፡ ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ ኢሕአዴግ ተሃድሶ ያስፈልገኛል ወደሚለው ድምዳሜ ሲደርስ መነሻ የሆነው ትንታኔ ነው፡፡

ትንታኔው ጥልቀት ሳይኖረው መፍትሔና ተሃድሶው ጥልቀት ሊኖረው አይችልም፡፡ እንደ ኢሕአዴግ ትንታኔና ግምገማ ለገባንበት የፖለቲካ ቀውስ ዋነኛው መንስዔ ባለሥልጣናት ከሕዝብ ጥቅም ይልቅ የራሳቸውን ጥቅም ማስቀደማቸው ነው፡፡ በፌዴራልና በክልል ከፍተኛ ኃላፊነት የተሰጣቸው ባለሥልጣናት ለተሰጣቸው ኃላፊነት ብቁ ካለመሆናቸውም ባሻገር፣ በሥልጣናቸው ሕዝብን ከማገልገል ይልቅ የግል ሀብት ማካበት ይመርጣሉ የሚለው የኢሕአዴግ ወቅታዊ አቋም ‹‹ተሃድሶ ያስፈልገናል›› ለሚለው የድርጅቱ ውሳኔ መነሻ ሆኗል፡፡

ኢሕአዴግ የሹማምንቱን አግባብ ያልሆነ የግል ጥቅም የማሳደድ አባዜና የብቃት ችግር ዘግይቶም ቢሆን ማመኑ መልካም ነው፡፡ ሆኖም ተሃድሶው በእውነትም ጥልቅ ተሃድሶ እንዲሆን በቅድሚያ የኢሕአዴግ ባለሥልጣናት እንዲህ ያለ ዝንባሌ የሚታይባቸው ለምንድነው ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ የሕዝብ ሀብት የሚመዘብሩና የጉቦ ቀበኛ የሆኑ ባለሥልጣናት ከላይ እስከታች የበዙት ለምን እንደሆነ ሳንረዳ ይህንን ችግር መቅረፍ አንችልም፡፡ ‹‹አለባብሰው ቢያርሱ ባረም ይመለሱ›› እንዳሉት ነው ነገሩ፡፡

እንደ እኔ አመለካከት የኢሕአዴግ ሹማምንት ዘንድ በስፋት የሚታየው በመንግሥት ሥልጣን የግልን ጥቅምና ሀብት የማደራጀት ችግር መንስዔ የሆኑ ሁለት ዋነኛ ምክንያቶች አሉ፡፡ በእርግጥም መንስዔዎቹ እነዚህ ብቻ ናቸው ባልልም ተደርገው ሊታዩ የሚችሉት እነዚህና ተያያዥነት ያላቸው ምክንያቶች ናቸው፡፡

አንደኛው ምክንያት ኢሕአዴግ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ የሕዝብ ድጋፍና ተቀባይነት የሌለው ፓርቲ መሆኑ ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ኢሕአዴግ የመንግሥትን ሥልጣን ለመገደብና ለመቆጣጠር አስፈላጊ የሆኑ ሕጋዊና ተቋማዊ መዋቅሮችን ክፉኛ ማዳከሙ ነው፡፡ ላለንበት ቀውስ መንስዔ ናቸው በማለት ከላይ ያስቀመጥኩዋቸውን እውነታዎች ለመረዳት ምርጫ 97ን ተከትሎ የሆነውን ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡ ሁላችንም እንደምናስታውሰው ምርጫ 97 በአንፃራዊነት የኢሕአዴግ ተፎካካሪ ፓርቲዎች የተሻለ ነፃነት አግኝተው ከኢሕአዴግ ጋር የተወዳደሩበት ምርጫ ነበር፡፡

የኢሕአዴግ መሪዎችም ከምርጫው በፊት ባደረጉት ‹‹ተሃድሶ›› እና በኢኮኖሚው ላይ በታየው መነቃቃት የተነሳ በምርጫው ሕዝብ ይደግፈናል ብለው በተስፈኝነት የገቡበት ምርጫ ነበር፡፡ ሆኖም የምርጫ ፉክክሩ ተጧጡፎና ተቃዋሚ ፓርቲዎችም በሕዝቡ ዘንድ ተቀባይነታቸው ከፍ እያለ መጣ፡፡ ምርጫውም እጅግ አወዛጋቢ በሆነ መልኩ ተጠናቀቀ፡፡ ከዚያ በኋላ ኢሕአዴግ በዴሞክራሲያዊ ዓውድ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር መወዳደርን እርም ብሎ ብቻውን ሮጦ ብቻውን ‹‹የሚያሸንፍበትን›› ዓውድ ለመፍጠር ሥራዬ ብሎ ተንቀሳቀሰ፡፡

በዚህ እንቅስቃሴ ውስጥ ኢሕአዴግ ከወሰዳቸው ዕርምጃዎች ውስጥ አንዱ የአባላቱን ቁጥር በብዙ እጥፍ ማሳደግ ነበር፡፡ ተቃዋሚዎች ሲታሰሩና ሲዋከቡ በአባልነት ለሚመለመሉ ደግሞ የተለያዩ መደለያዎች ቀረቡ፡፡ ሥራ፣ ትምህርት፣ ብድርና ሌሎችም በመንግሥት ‹‹ችሮታ›› የሚገኙ ጥቅምና ዕድሎች ለፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ብቻ የሚሰጡ ሆኑ፡፡

ኢሕአዴግ ብዙዎችን በጥቅም አባብሎ አባላቱ አደረገ፡፡ ይህ የቅርብ ጊዜ ታሪካችንና ብዙዎቻችን ያየነውና የማንካካደው ነገር ይመስለኛል፡፡ የፓርቲ አባላት ያልሆኑት ሲገፉ የፓርቲ አባል ለሆኑና ‹‹ንቁ ድጋፍ›› ለሚሰጡ ደግሞ በምላሹ ኑሮ ሲመቻች፣ ሲደላደል ታየ፡፡ ታዲያ ኢሕአዴግ በዚህ ሒደት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አባላት ሰብስቦ፣ እነዚህን አባላቱን ሹመት ሰጥቶ ሲያበቃ ʻየግል ጥቅም አሳዳጅ ናቸውʼ ብሎ ማማረሩን ምን ይሉታሉ? እንክርዳድ ዘርቶ ስንዴ አይታጨድም፡፡

በአገር ደረጃ ነፃ ህሊናን ጠላት አድርጐ በአበል፣ በሥራ ዕድል፣ በትምህርት ዕድል፣ በሥልጣንና በጥቅም ደልሎ ብዙዎች ያላመኑበትን ‹‹አሜን!›› እንዲሉ ያደረገ ፓርቲ አባላቱ ‹‹እበላ ባይ›› ሆነው ቢገኙ ሊገረም አይገባም፡፡ የነፃነትና የዴሞክራሲ ዕጦት፣ አምባገነንነትና ጭቆና አድርባይነትን በእጅጉ ያስፋፋሉ፡፡ አስመሳይና እበላ ባዩ እንዲህ ባለው ሥርዓት ከፍ ከፍ እያለና እየተመቸው ይሄዳል፡፡ ኢሕአዴግ በተለይም ከምርጫ 97 በኋላ ጉልበትና እበላ ባይነትን የሥልጣኑ ምሰሶዎች አድርጐ ቆይቷል፡፡ በዴሞክራሲያዊ ፉክክር የተገኘ የሕዝብ ይሁንታ ስለሌለው ደጋፊና አባል የሚያስጠጋውና የሚሰበስበው በሥልጣን ተጠቅሞ ሀብት የማጋበስ ዕድል እየሰጠ ነው፡፡

በተለይም ለኢሕአዴግ ተቃውሞ በሚበዛባቸው ክልሎች የኢሕአዴግ አካል መሆን የራሱ የሆነ ማኅበራዊ ዋጋ የሚያስከፍል፣ የሚያስነቅፍና የሚያስተች ነበር፡፡ ይህንን ሁሉ ውግዘት አልፈውና ችለው ብዙዎች የድርጅቱ አባል እንዲሆኑ ኢሕአዴግ ለአባላቱ ሥልጣናቸውን ለግል ጥቅማቸው እንዲያውሉ መፍቀድ ነበረበት፡፡ በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ ድርጅቱና አባላቱ የተዋዋሉት ውል አባላቱ ባያምኑበትም ኢሕአዴግ እንዲደግፉ ሲያስገድድ፣ ሕዝብ በድለውም ቢሆን ሀብት እንዲያካብቱ ‹‹መብት›› ሰጥቷቸዋል፡፡

መሬት እንደ ከረሜላ የቸረቸሩት ሹመኞች ኢሕአዴግ አባል ሲያደርጋቸው አባል የሆኑት ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ ጥሟቸው ወይም ኢሕአዴግ እኔ ለወጣሁበት ሕዝብ የሚያስብና የሚጨነቅ፣ የሚጠቅም ፓርቲ ነው›› ብለው አይደለም፡፡ እየበላህ ደግፈኝ የሚለውን ግብዣ ሲታደሙ ህሊናን ከቤት ትተው ነው፡፡

ስለዚህ ኢሕአዴግ ጥልቅ ተሃድሶ ለማድረግ እውነት ከወሰነ ለእበላባይነት ፖለቲካ ምቹ የሆነውን አምባገነናዊ ዓውድ ማስወገድ አለበት፡፡ በአሁኑ ጊዜ አድርባይነት ከዋነኞቹ የኢሕአዴግ የሥልጣን ምሰሶዎች አንዱ ነው፡፡ ሌላኛው ዋነኛ ምሰሶ ጉልበት ነው፡፡ ይህ እውነታ ካልተለወጠ ሹመኛና ባለሥልጣን ቢለዋወጥም ችግሩ ይቀጥላል፡፡ አገሩ ነፃ ካልሆነ፣ የዜጐች መሠረታዊ የዜግነት መብትና ነፃነቶች ካልተከበሩ፣ የሥልጣን ምንጭ በእውነትም የሕዝብ ይሁንታ ካልሆነ፣ ካለንበት ቀውስ አንወጣም፡፡ የ‹‹ተሃድሶው›› አቅጣጫ ከሹም ሽር አልፎ ወደ ችግሩ ሥር፣ ወደ ዋነኞቹ መንስዔዎች የሚያስኬድ መሆን አለበት፡፡ ሕዝቡ በመረጠውና በወደደው የሚተዳደር ካልሆነ፣ ነፃነቱን እንደተነፈገ ከቀጠለ ያለንበት ቀውስ እየባሰ ይሄዳል፡፡

የሕዝብ ይሁንታ የሌለው መንግሥት ጥቂቶችን በጥቅም ገዝቶ፣ ብዙኃኑን አስፈራርቶ ከመኖር ውጪ አማራጭ የለውም፡፡ በቅርቡ እንዳየነው ደግሞ ይህ አካሄድ፣ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ሰፊ የብሔር ብዝኃነት ባለበት አገር የሚያዛልቅ አይደለም፡፡ በጥቅም የተገዙት እየተገባበዙ፣ እየዘረፉ፣ ሕዝብን እያማረሩና እየበደሉና የመሳሰሉትን እየፈጸሙ አመፅ ይበዛል፡፡ ስለሆነም ከቀውሱ ለመውጣት እበላ ባዮች ላይ ከመዝመት በፊት እበላ ባዮችን ያበዛውን አምባገነናዊ ዓውድ መለወጥ ያስፈልጋል፡፡ ይህ ዓውድ ሲለወጥ ታዲያ የፓርቲውን የሥልጣን ሞኖፖል ማሳጣቱ የማይቀር ነው፡፡ ታዲያ ፓርቲው አባላቱን ከግል ጥቅማችሁ ይልቅ የሕዝብ ጥቅምን አስቀድሙ ብሎ እንዳሳሰበ፣ ፓርቲውም ከድርጅቱ በሥልጣን ከመቆየት ፍላጐት ይልቅ የአገር ጥቅምና ህልውና ካስቀደመ ሥልጣኑን ከተፎካካሪዎቹ ቢጋራ ቅር ሊሰኝ አይገባውም፡፡ የተሃድሶው ጥልቀትና ሀቀኝነት መለኪያ ይኼ ነው፡፡ ካልሆነ ቀደም ብዬ እንዳልኩት ‹‹አለባብሰው ቢያርሱ ባረም ይመለሱ›› ነው ነገሩ፡፡

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊው የሕገ መንግሥት ኤክስፐርትና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት መምህር ሲሆኑ፣ ጽሑፉ የእሳቸውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ በኢሜይል አድራሻቸው gediontim@gmail.comማግኘት ይቻላል፡፡  

 

 

 

Standard (Image)

እውን በኢትዮጵያ ሴም የሚባል ሕዝብ አለ?

$
0
0

በብርቱካን ወለቃ

በዓለም ላይ  የሥነ ሰብ ተመራማሪዎች የዓለምን ሕዝብ ጥቁር፣ ነጭ፣ ቢጫ፣ቀይ ከማለት አልፈው ሴም፣ ኔግሮይድ፣ ከውኮሴድ እያሉ ይመድቧቸዋል፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ደግሞ የኖኅ ልጆች በመባል የሚጠሩት ሴም፣ ካምና ያፌት ይባላሉ፡፡ ከካም ልጆች ኩሽ ጥቁር ሕዝቦች እንደሆኑ ይነገራል፡፡ አሠፋፈራቸውም አፍሪካና አካባቢው መሆኑ ይነገራል፡፡

ይሁን እንጂ ከዚህ ሃይማኖታዊ ትውፊትና የሥነ ሰብ ምርምር ውጭ የተለያዩ ግለሰቦች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የፖለቲካ አጥኚዎች በተለያየ ጊዜ ስለኢትዮጵያ ሕዝቦች የተሳሳተና የተዛባ መረጃዎችን በማደባለቅ ሲጽፉና በቤተ እምነቶች ጭምር ሲያስተምሩ ቆይተዋል፡፡

ሌላ ሌላውን ትተን በ13ኛው ክፍለ ዘመን በመጀመሪያ በግሪክ ቋንቋ ቀጥሎ በዓረብኛ ቀጥሎ ወደ ጀርመን ከዚያ ወደ ግዕዝ በቅብብሎሽ የተጻፈውና የተተረጎመውን ጸሐፊዎች የራሳቸውንና የንጉሣቸውን ፍላጎት እየጨማመሩ የጻፉት ክብረ ነገሥት (Glory of Kings) የሚባለው የተረት መጽሐፍ፣ በኢትዮጵያ ሕዝቦች የተዛባ የማንነት ቀውስ እንዲፈጠር ምክንያት ከሆኑት ምንጮች አንዱ ነው፡፡ ይህ የተረት መጽሐፍ የግሪኩ ትርጉም ከዓረብኛው፣ የዓረብኛው ከጀርመኑ፣ የጀርመኑ ከግዕዙ እጅግ የተለያየ ነው፡፡ ለምን ተጻፈ፣ በማን ተጻፈ የሚለውን በሌላ ጊዜ የምመልስበት ሆኖ በዋናነት ግን ሥልጣንን ከዛግዌ ሥርወ መንግሥት ወደ ሰለሞናዊው ተብየ ሥርወ መንግሥት በሐሰት ለማስተላለፍ የተጻፈ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡

ሃይማኖታዊ ዲስኩር የተጨመረበት ሥልጣን በእግዚአብሔር ጭምር ለተፈቀደላቸው የእስራኤል ወገን ለሆኑት የሰለሞን ዘሮች ብቻ የተሰጠ ነው በሚል የአገው ሕዝቦች መንግሥታዊ ሥልጣናቸውን አስረክበው አለት በመቆርቆር ቤተ ክርስቲያን ማነፃቸውን ተያያዙት፡፡ የንግሥት ሳባ የንጉሥ ሰሎሞን ጥበብ ለማየት ጓጉታ ለጉብኝት በሄደችበት ኢትዮጵያዊቷ ንግሥት በንጉሡ ተደፍራ እንድታረግዝና ወንድ ልጅ እንድትወልድ ተደርጎ የተተረተው ተረት እውነት ሆኖ ሳይሆን፣ የግድ የነጮችና የዓረቦች ተንኮል ኢትዮጵያን ከአናቷ በመቆጣጠር ዓባይ ያለምንም ከልካይ ወደ ግብፅ እንዲፈስ ለማድረግ የተሸረበ ሴራ ነበር፡፡ ለዚህ ዓለማቸው ያግዝ ዘንድ በክርስትና ማስፋፋት ስም የኢትዮጵያን ማንነት ከኩሽ ወደ ሴሜቲክ መቀየር የግድ አስፈላጊ ነበር፡፡ ዓረብና እስልምና እንዳይቀላቀልባችሁ፡፡

ለዚያ ይረዳ ዘንድ ሳባ በሰሎሞን መደፈር ነበረባት፡፡ ከዚያ ወንድ ልጅ መውለድ ነበረባት፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ ያ ከሰለሞን ተወለደ የሚባለው ‹‹ቀዳማይ ምንሊክ›› ከ20 ዓመት በኋላ ወደ አባቱ አገር መሄድ ነበረበት፡፡ ከዚያም ከእስራኤል ወገን የሆኑ 12 ሺሕ አጃቢዎች የራሳቸውን ታቦተ ጽዮን ሰርቀው ወደ ኢትዮጵያ  መምጣት ነበረባቸው፡፡ንጉሥ ሰለሞን በማይገዛት አገር ኢትዮጵያ ልጁን ‹‹ንጉሠ ነገሥት ሞዓ አንበሳ ዘ ዕምነ ነገደ ይሁዳ›› ብሎ መሾም ነበረበት፡፡ አስቡት ይህ የሰለሞን ልጅ ተብየው መሾም እንኳ ካለባት የመሾም ሥልጣን ያላት ንግሥት ሳባ እንጂ፣ ንጉሥ ሰለሞን ሲጀመር በኢትዮጵያ ልጁን ንጉሥ አድርጎ ለመሾም ምንም ዓይነት ሥልጣን አልነበረውም፡፡ የውሸቱ የካብ ድርድር ከዚህ ላይ ይናዳል፡፡

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ኢትዮጵያን የሴም ምድር የማድረጉ ዘመቻ ከቤተ መንግሥት እስከ ቤተ እምንት ድረስ ተሰበከ፡፡ የሰሜኑ ኩሽ ሕዝብ (አገው) እየተንደረደረ ራሱን ከኩሽ ወደ ሴሜቲክ ‹‹ቀይሬያለሁ›› በማለት በውሸት ጉራ ተነፋ፡፡ ሴሚቲክ ነኝ ማለት ምድራዊ ሥልጣን በር ከማስከፈት አልፎ ሰማያዊ ቤተ መንግሥትም ወራሾች እኛ ብቻ ነን እንዲሉ አስባላቸው፡፡ ይህን የውሸት ማንነት ያልተቀበለውን ሕዝብ ከቦታው በማፈናቀል ማፍለስ ተያያዙት፡፡ የኢትዮጵያ መሬት ከባለቤቱ ወጥቶ በቤተ መንግሥትና በቤተ ክርስቲያን ቁጥጥር ሥር ዋለ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በሰሜንና በሰሜን ምዕራብ የሚገኙ ሕዝቦች ሙሉ በሙሉ በማንነት ቀውስ ውስጥ ወደቁ፡፡ የውሸት ማንነት ቀድመው የወሰዱት ባልተቀበለው ላይ የስድብ ናዳ ማውረድ ጀመሩ፡፡ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረ ሰው ‹‹ከእንጨት ተገኘ›› በማለት በቤተ ክርስቲያን ጭምር ተሰበከ፡፡ የጽድቅን በር ቁልፍ በእነሱ እጅ የተያዘ እስኪመስል ድረስ ማንነቱን ያልቀየረ ሕዝብ ገሀነም ገቢ ነው ብለው አስተማሩ፡፡

ከመሬታቸው የተፈናቀሉ አገዎች ‹‹ፈላሻ›› ተብለው መሬት አልባ በመደረጋቸቸው በብረት ቅጥቀጣ፣ በሸማ ሥራ፣ በሸክላ ሥራ በመሰማራት ኑሯቸውን እንዲገፉ ተገደዱ፡፡ ማንነታቸውን ቀይረው መሬታቸው ያልተነቀሉትም ቢሆን በጭሰኝነት እንዲማቅቁ ተደረገ፡፡ ጎንደር ቋራ፣ ወገራ፣ አርማጭሆ የነበሩ የአገው ክፋይ የሆኑ ሕዝቦች የዚህ ታሪካዊ በደል ሰለባ እንዲደረጉ ሆነ፡፡  በደንቢያ፣ በአለፋ፣ በቋራ፣ በአርማጭሆ በከፊል ጭልጋ በጐንደር ዙሪያ በበለሳ ይኖሩ የነበሩ ቅማንቶች ሳይወዱ በግድ ሴሜቲክ ነኝ ብለው በመሬታቸው እንዲቀመጡ ሲደረግ ማንነታችን እንቀይርም ያሉ ከጐንደር በከፊል ተገፉ፡፡ በመሬታቸው ላይ አስከ 1966 ዓ.ም ድረስ ጭሰኛ እንዲሆኑ ተደረጉ፡፡ በተለምዶ ቤተ እስራኤል የሚባሉ የአገው ሕዝቦች ፈላሻ ተብለው በመጨረሻ ከእናት ምድራቸው ጐንደር እንዲለቁና ወደማያውቁት አገር እንዲሰደዱ ተገደዱ፡፡

የሰሜንና የሰሜን ምዕራብ ሕዝቦች በውሸት የበላይነትና የበታችነት ቀውስ ውስጥ ተዘፈቁ፡፡ ቀድሞ ክርስትናን የተቀበለው ባልተቀበለው ላይ ጦርነት አወጀ፡፡ ወንድም በወንድሙ ላይ ዘመተ፣ ወንድም ውንድሙን ናቀው፡፡ ኢትዮጵያን ዘንግተው ገዥዎችና ተከታዮቻቸው እኛ ‹‹ከእስራኤል ወገን የሆን ሴማዊ ነን›› ብለው ታበዩ፣ ሌላውን ሕዝብ ናቁ፡፡ የጎጃምና የበጌ ምድር ጋፋት ሕዝቦች ቀድመው ማንታቸውን ከለወጡትና በሌላው ሕዝብ ላይ የበታችና የበላይ የሚል ስብከታቸውን ተያያዙት፡፡ በተለይ ጋፋቶች ቀድመው ቤተ ክርስቲያን ውስጥና ቤተ መንግሥት በመሰግሰግ በአገው ሕዝቦች ላይ ይቅር የማይባል ግፍ ፈጸሙ፡፡ በቤተ ክርስቲያን ላይ ቆመው የአገው ሕዝብ በእግዚአብሔር ፊት ጽድቅ አያገኝም አሉ፡፡

ይህ የማንነት ቀውስ ዛሬም ድረስ በመቀጠሉ አንድን ሕዝብ ሌላኛው በመናቅ በመሳደብ ቀጥሏል፡፡ በዚህ የማንነት ቀውስ ውስጥ ያልወጡ ቡድኖች ዛሬም ወገናቸውን ከማሳደድ አልተመለሱም፡፡  ሲፎክሩና ሲያቅራሩ እንትን ገዳይ፣ የእንትን ዘር እንትን ገዳይ፣ እንትን በሊታ በማለት ሳይፈሩ ይናገራሉ፡፡ ይህ ዓይነት አስተሳሰብ ጐንደር ላይ በግልጽ በሐምሌ 2008 ዓ.ም. በግልጽ በአደባባይ ተነግሯል፡፡ እነዚህ ሰዎች ዛሬም ሳያፍሩ በሕዝብ ላይ ጸያፍ ንግግር ይናገራሉ፡፡

ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶለሳ የሚባሉ ግለሰብ በኢትዮጵያ ሴም የሚባል ሕዝብ እንደሌለ ከስንት ዓመት በኋላ ይህን ሀቅ ለመጻፍ ተንደረደሩ፡፡ ‹‹ሴሜቲክ የሚባል ሕዝብ በኢትዮጵያ ምድር የለም፡፡ ሁሉም የኩሽ ዘር ነው›› አሉ እኚህ ግለሰብ ፈረንጆች  ከመቅረት መዘግየት ይሻላል እንደሚሉት አባባል ሀቁን መናገራቸው መልካም ቢሆንም፣ ድሮ የሚያውቁትን ሀቅ በዚህ ወቅት መጻፍ የፈለጉበት የራሳቸው ፖለቲካዊ አጀንዳ ያነገበ ለመሆኑ አያጠያይቅም፡፡ ቢሆንም እንኳንም እየመረራቸውም ቢሆን ሀቁን ተናገሩት፡፡ አስታውሳለሁ እኚህ ፕሮፌሰር በአንድ ወቅት በ2004 ዓ.ም. አካባቢ በኢትዮ ሚዲያ ድረ ገጽ የጻፉት ጽሑፍ መቼውንም ቢሆን አልረሳውም፡፡ አንድን ብሔር ለይተው ‹‹አገር አቅኝ›› ሌላው ግን መጤና ተጠማኝ፣ ይህ እሳቸው የሚያሞግሱት ሕዝብ የሚናገረው ቋንቋ ምርጥ፣ ሲናገሩት ጉሮሮ የማይከረክርና የማይከብድ አድርገው የጻፉት ጽሑፍ አሁን ካሳተሙት መጽሐፍ ጋር ምንም የማይገናኝና አሁን የጻፉት መጽሐፍ ለምን ታስቦ እንደተጻፈ መገመት አያዳግትም፡፡ ግን እንኳንም ጻፉት፡፡

ዞሮ ዞሮ ከ14ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በኢትዮጵያ የተሰበከው የተሳሳተ የማንነት ቀውስ ዘመን ተሻግሮ ዛሬ ድረስ  ኢትዮጵያን እያተራመሳት ይገኛል፡፡ በተለይ በሰሜን አካባቢ የሚነሱ ተደጋጋሚ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምንጫቸው በውጭ ኃይሎች የሚደገፍ የዚህ የማንነት ቀውስ ውጤቶች ናቸው፡፡ ኤርትራ ለመገንጠል እንደ ምክንያት የተጠቀመችበት የማንነት ቀውስ የወለደው ‹ዓረባዊ አፍሪካዊ›› አስተሳሰብ ጭምር ነው፡፡

ኢትዮጵያ እንደ አገር ጠንካራ ሆና ለመቀጠል በመጀመሪያ ደረጃ ይህ የማንነት ቀውስ ሊስተካከል ይገባል፡፡ ከዚያ በኋላ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሲርቅ የአንድ የአዳም ልጆች፣ ሲቀርብ ደግሞ የአንድ ቤተሰብ የኩሽ ልጆች መሆናቸውን በመገንዘብ አንዱ በማንነት ቀውስ ተዘፍቆ ሳይታበይ ወይም ሳይጠብ በጋራ በፍቅር መኖር ይቻላል፡፡

ለዚህ ደግሞ መንግሥት ትክክለኛ የሕዝቦች ታሪክን ለአዲሱ ትውልድ በማስረጽ የኢትዮጵያን አንድነት በጠነከረ መንገድ ማስቀጠል ይቻላል፡፡ ያለፉ የመናናቅ ታሪኮችና የሃይማኖት ስብከቶች ሊስተካከሉ ይገባል፡፡ የታሪክ ትምህርት ክፍሎችን በመዝጋት ሕዝብን ታሪክ አልባ ከማድረግ ይልቅ ትክክለኛ የሕዝብ ታሪኮችን ማስተማር የበለጠ መቀራረብን ያመጣል፡፡ ኢትዮጵያ ታሪካዊ ሕዝቦች ያላትና ሰፊ ታሪክ ያላት ቢሆንም፣ ይህ ሀቅ ተዛብቶ ሲተረት እንደነበር ይታወቃል፡፡ ማስተካከል ግን ይቻላል፡፡

በሌለ ማንነት ከመኮፈስ ይልቅ እውነተኛ ማንነትን ተገንዝቦ ኅብረት መፍጠሩ መልካም ነው፡፡ እንደ ሕዝብ ሴም የሚባል ሕዝብ በኢትዮጵያ ምድር ላይ ባይኖርም የዓረብ የሚመስሉ ‘ኤለመንቶች’ ግን በኢትዮጵያ ምድር ላይ ይታያሉ፡፡ ይህ ማለት ግን ንጉሣችን አጼ ኃይለ ሥላሴ አሉ እንደሚባሉት እኛ ሴም ነን ማለት እንዳልሆነ ሁሉም ሆዱ ያውቀዋል፡፡

ከአዘጋጁ፡-ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካካት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው birtuwoleka2015@gmail.comማግኘት ይቻላል፡፡

 

 

Standard (Image)
Viewing all 231 articles
Browse latest View live